ሰኞ, ዲሴምበር 03, 2012

ቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ

ማሽላና ስንዴ በአንድ አብረን ስንቆላ፤
እያረረ ሳቀ የባህር ማሽላ፡፡

ከሰል የሚሆኑ ብዙ እንጨቶች ሳሉ፤
ዝግባ ለምን ይሆን ይቆረጥ የሚሉ፡፡


         የሰማይ አሞራ ልጠይቅሽ ወሬ፣
         ተቃጥሏል መሰለኝ ሸተተኝ አገሬ፡፡

       
         ለጌሾ ወቀጣ ማንም ሰው አልመጣ
         ለመጠጡ ጊዜ ከየጐሬው ወጣ፡፡

         ቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ከተውኔት ድርሰታቸው በተጨማሪ መዝሙሮችንና ግጥሞችን ደርሰዋል፡፡ የኢትዮጵያ አንድነትና የህብረት መዝሙር የሚገልጽልንን የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር (ተፈሪ ማርሽ)፣ ወላድ ኢትዮጵያ፣ አጥንቱን ልልቀመው፣ ድንግል አገሬ ሆይ የሚባሉ መዝሙሮችን ደርሰዋል፡፡ አጥንቱን ልልቀመው የሚለው ግጥም አርበኞቹን የዶጋሊውን አሉላ አባ ነጋ እና ራስ ጎበናን በማነፃፀር የገጠሙት ግጥም ሲሆን ድንግል ሀገሬ ሆይ የተሰኘውን ድርሰት የፃፉት በስደት ኢሊባቡር ሆነው በ1929 ዓ.ም ነበር፡፡ ይህ መዝሙር ከመጀመሪያ ረድፍ ከሚጠቀሱት ስራዎቻቸው ቀዳሚው ነው፡፡

             ድንግል ሀገሩ ሆይ ጥንተ ተደንግሎ
             ጥንተ ተደንግሎ ጥንተ ተደንግሎ
             ህፃናቱ ታርደው ያንቺም ልብ ቆስሎ
             ልጅሽ ተሰደደ አንቺን ተከትሎ
             የህፃናቱ ደም አዘክሪ ኩሎ፡፡
             አዝማች፤ አስጨነቀኝ ስደትሽ
             እመቤቴ ተመለሺ እመቤቴ ተመለሺ


ይሄ ግጥም ዮፍታሄ ንጉሴ ህዝቡ በፋሺስት ወረራ የደረሰበትን ስደት የገለፁበት ስንኝ ነው፡፡ ቅድስት ድንግል ማርያም ከእስራኤል ወደ ግብጽ ያደረገችውን ስደት እና በኤሮድስ ህፃናት መቀላታቸውን ከኢትዮጵያ ስደት ጋር ያነፃፀሩበት ግጥምም ነው፡፡ የቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ግጥሞች ትንቢታዊ ሲሆኑ በአንድ ስንኝ የሚጽፉት ግጥም ተሰጦአቸው የላቀ መሆኑን ያሳየናል፡
የቀኝ ጌታ ዮፍታሄ አፃፃፍ ለተከታዮቹ ደራሲያን ምሳሌ ስለነበር አንጋፋነታቸው ታላቅ ዋጋ የሚሰጠው ነው፡፡ ዮፍታሄ በግእዝ ቅኔ የበሰሉ ስለነበሩ አማርኛ የስነ ጽሑፍ ቋንቋ እንዲሆንና እንዲያድግ የላቀ አስተዋፅኦ አበርክተዋል፡፡

     የአማርኛ ስነ ጽሑፍን ለማሳደግ በተውኔት፣ በግጥም፣ በዘፈን እና በመዝሙር ባደረጉት ጥረት በኢትዮጵያ ስነ ጽሑፍ ታሪክ ውስጥ ከፍተኛ የክብር ቦታ አላቸው፡፡ ባለ ቅኔው ዮፍታሄ ከጣሊያን ወረራ በኋላ እስከ 1941 ዓ.ም የህግ መወሰኛ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው ሲሰሩ ቆይተው በ1942 ዓ.ም አርፈዋል፡፡ የባለ ቅኔው ዮፍታሄ ስራዎች ግን ተጽእኖ ፈጥረው ከትውልድ ወደ ትውልድ ይሸጋገራሉ፡፡

ቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ  ሥራዎች:--

1. እኔ አይኔን ሰው አማረው (ግጥምና ቅኔ)
2. ዐጥንቱን ልልቀመው፥ መቃብር ቆፍሬ (ግጥምና ቅኔ)
3. ወላድ ኢትዮጵያ ለልጆቿ ብላ (ግጥምና ቅኔ)
4. ጎበዛዝቴ ሆይ ወይ ቆነጃጅቴ (ግጥምና ቅኔ)
5. ሰውን ሰው ቢወደው አይኾንም እንደራስ (ግጥምና ቅኔ)
6. አወይ ጥርሴ ሞኙ ዘወትር ይሥቃል (ግጥምና ቅኔ)
7. ሙናዬ (ግጥምና ቅኔ)
8. የኛማ ሙሽራ (ግጥምና ቅኔ)
9. አንተ ባለጐዛ (ግጥምና ቅኔ)
10. ድንግል አገሬ ሆይ ጥንተ ተደንግሎ (ግጥምና ቅኔ)
11. የእኛማ ሀገር (ግጥምና ቅኔ)
12. ሰለኢትዮጵያ (ግጥምና ቅኔ)
13. ትንሽ ዐማርኛ (ግጥምና ቅኔ)
14. የሥነ- በዓል መዝሙር...እንደመፋቂያ (ግጥምና ቅኔ)
15. ጉሰማዬ (ግጥምና ቅኔ)
16. ተነሱ ታጠቁ (ግጥምና ቅኔ)
17. አብሪ ብርሃንሽን (ግጥምና ቅኔ)
18. የባሕር ዳር ጨፌ (ግጥምና ቅኔ)
19. ባገር ገዳይ፥ቋጥኝ ድንጋይ... (ግጥምና ቅኔ)
20. በለስ ለመለመች (ግጥምና ቅኔ)
21. እስክትመጣ ድረስ... (ግጥምና ቅኔ)
22. ጎሐ ጽባሕ (ግጥምና ቅኔ)
23. አገሬ ኢትዮጵያ...ሞኝ ነሽ ተላላ... (ግጥምና ቅኔ)
24. የኢትዮጵያ ሕዝብ መዝሙር (ግጥምና ቅኔ)
25. የሰንደቅ ዓላማ መዝሙር ደሙን:ያፈሰሰ፥ተጣማጅ: አርበኛ (ግጥምና ቅኔ)
26. አፋጀሽኝ (ተውኔት)
27. እያዩ ማዘን (ተውኔት)
28. ስለአያ ከምሱና ስለአያ እነባንት ይቀጡ (ተውኔት)
29. እለቄጥሩ /ጎበዝ አየን /  (ተውኔት)
30. ጥቅም ያለበት ጨዋታ (ተውኔት)
31. የሕዝብ ፀፀት፥የእመት በልዩ ጉዳት (ተውኔት)
32. የሆድ አምላኩ ቅጣት (ተውኔት)
33. ዕርበተ ፀሐይ (ተውኔት)
34. ምስክር (ተውኔት)
35. ያማረ ምላሽ (ተውኔት)
36. ዳዲቱራ (ተውኔት)
37. ሞሽሪት ሙሽራ (ተውኔት)
38. መሸ በከንቱ፥ ሥራ ለፈቱ (ተውኔት)
39. ጠረፍ ይጠበቅ (ተውኔት)
40. ዓለም አታላይ (ተውኔት)
41. የደንቆሮዎች ትያትር (ተውኔት)
42. ንጉሡና ዘውድ (ተውኔት)




        ምንጭ:-- http://mekilit.blogspot.com/2014/02/1885.html





ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ማሞ ካቻ (አቶ ማሞ ይንበርብሩ)

  አቶ ማሞ ይንበርብሩ (ማሞ ካቻ) እስቲ እናስታውሳቸው፣ ተቀብሮ እንዳይቀር አኩሪ ታሪካቸው  (ደረጀ መላኩ)   አቶቢሲ ማሞ ካቻ የት ትሄዳለህ? ገብረ ጉራቻ… ታዳጊው ማሞ ይንበርበሩ ገና በጨቅላ እድሜው አባቱ አቶ...