እሑድ, ኖቬምበር 25, 2012

ኢትዮጵያን ከእግዚአብሔር እጅ እንሻት


 (ሰኔ ፲፱፻፺፯ ዓ. ም.)
 
በ፲፱፻፹፫ ዓ.ም. ብዙ ሆነን ከአሰብ ተሰድደን በጅቡቲ በኩል ለማለፍ ስንሞክር የፈረንሳይ ወታደሮች አንድ ሜዳ ላይ አገቱን። እጅግ በጣም ሐሩር ስለነበር ከመንገላታት ጋር አንዳንዶቻችን በብርቱ ታመን ነበር። ከፊት ለፊቴ ቆሞ በጠላትነት አይን እያየ፣ በመሣሪያው እያስፈራራ፣ አንዳንዴም እየገፈተረ፣ መተላለፊያ የሚከለክለኝን ወጣት ፈረንሳዊ እያየሁ በሃሳብ ሰመጥኩ። እኔን የሚመስሉ ዘመዶቸ በሚኖሩበት መሬት እንዳላልፍ ከፈረንሳይ አገር መጥቶ ከለከለኝ ። መሰደዴ ደግሞ እሱን የሚመስሉ ሰዎች ባዘጋጁት ውጥን ነው። ይህ ወጣት ከሩቅ አገር መጥቶ በሰፈሬ እንዳላልፍ የከለከለኝ በጠማማ መንገድ ከሚሄድ ባለጠጋ ያለነውር የሚሄድ ደሀ ይሻላል ተብሎ እንደተጻፈው አባቱ ከሩቅ አገር መጥተው በአራጣ ብዛትና በቅሚያ የአባቴን ስለወሰዱ አይደለምን? ታዲያ ይህ ፈረንሳዊ ካባቱ አንድ ጊዜ ባገኘው አስነዋሪ ትርፍ ምክንያት የሱ ልጅ ከሩቅ አገር መጥቶ የሰው መብት ከልካይ፤ የኔ ልጅ ደግሞ በራሱ ሰፈር መብቱ የተዋረደ መሆኑ አይደለምን? ብየ አሰብኩ። ብዙ ሰው እንደዚህ አለማሰቡ መልካም ሆነ እንጂ ነገሩ መንፈስን የሚያውክ ነገር ነው። ከዚህ በሁዋላ ብዙወችን ነገሮች ሳያቸው ስለማናውቀው ነው እንጂ እኛ ፈልገን የምናመጣው የስብእና ውርደት በብዙ መልክ እንዳለ ተገነዘብኩ። እባካችሁ አገራችን ውስጥ ያለውን መንግሥት ቀይሩልን ብሎ ሌሎችን አገሮች ደጅ መጥናት እራሱ ውርደት ነው። በአገር ውስጥ፣ በቤተመንግሥቱ፣ በየመንገዱ፣ በየምግብ ቤቱ፣ በየመጠጥ ቤቱ፣ በየህዝብ አገልግሎት ተቅዋሙ የውጭ አገር ሰው ሲከበር ኢትዮጵያዊ ግን በኢትዮጵያውያን ዘንድ ተንቆ ማየት ውርደት ነው። ከኢትዮጵያዊ አዋቂወች ወይም ከአዛውንቶችዋ ምክር ይልቅ ኢትዮጵያን ጥቂት ቀን ጎብኝቶ ወይም በቴሌቪዢን አይቶ "ለኢትዮጵያ ችግር መፍትሔው ይሄ ነው" ብሎ የውጭ አገር ሰው የሚጽፈውን እያስተጋቡ መኖር ውርደት ነው። ከሊህቅ እስከ ደቂቅ ከኢትዮጵያዊነት ይልቅ የውጭ አገር ሰው መምሰልን መፈለግ ውርደት ነው። ስለኢትዮጵያ ችግር፣ ለችግሮችዋም መፍትሄ ይሆናል የሚለውን መልዕክቱን ሁሉም ሰው ሊያሰማ የሚፈልገው ለውጭ አገር ሰወች እንጅ ለኢትዮጵያውያን አለመሆኑ ውርደት ነው። ተማሪው እስከ መምህሩ፣ ልጅ እስከ አባቱ፣ ዲያቆኑ እስከ ጳጳሱ ድረስ አገርን ለቆ መሄድን መሻታቸው ለኢትዮጵያውያን ውርደት ነው።  አገርን ለቆ በውጭ አገር ለመኖር ከመፈለግ ብዛት ካህናት እንኩዋን ሳይቀሩ በየኤንንባሲው የሃሰት ምክንያትና ኑዛዜን ማቅረባቸው ውርደት ነው።  

በህሊና አስቦ በውን አመዛዝኖ መሥራትም ከቀረ ውሎ አድሮአል። የውጭ አገር ሰዎች ያሉትን እንደገደል ማሚቶ መልሶ መላልሶ ከማስተጋባት ብዛት እግዚአብሔር ያለጭንቅላት የፈጠረን እያስመሰልነው ነው። አንድ ጊዜ በውጭ አገር የቲዮሎጅ ትምህርት የማስትሬት ዲግሪ አግኝቻለሁ ብለው ኢትዮጵያ ካገኙት የክህነት ትምህርት ይልቅ በማስትሬቱ ዲግሪ የሚኮሩ አንድ ካህን "ኢትዮጵያ የሰው ልጅ መጀመሪያ የተገኘባት መሆንዋ በሳይንስም ተረጋግጥዋል" ብለዉ ስብከታቸውን "በሉሲ" ታሪክ ሲጀምሩ ትዝ ይለኛል። የፈረንጆቹ ትምህርት "ሉሲ ሰው መሆን የጀመረች ዝንጆሮ ናት" እንደሚል ካህኑ አላወቁም። ፈረንጅ የተናገረውን ያለጥያቄ ማስተጋባት ባህል እየሆነ ስለመጣ ፈረንጅ ከተናገረው እሱኑ መውሰድ እንጅ እሳቸው ምን በወጣቸው ምስጢሩን ይመርምሩ? ይህ ምሳሌ ነው፤ ይሁን እንጂ ከመቶ አመት ወዲህ የተወለደ ኢትዮጵያዊ እንደካህኑ "የምሠራውን፣ የምበላዉን፣ የማስበውንና የምናገረውን ነገር ፈረንጅ አዘጋጅቶ ይስጠኝ" የሚል ነው።
የራሳችን የሆነውን ማን ወሰደው?

የችግሩን ተፈጥሮ ለመንገር በሺህ የሚቆጠሩ ጽሁፎች በመቶ የሚቆጠሩ ጉዳዮችን በማንሳት ተግሣጽና ወቀሳን ሲያደርጉ ይሄው ሃምሳ አመት ሊሞላ ነው። ሁሉም በየተራው የችግሩ ምንጭ "ንጉሣዊ አገዛዝ፣ መሬት ያራሹ አለመሆን፣ ፊዩዳሊዝም፣ ቡርዥዋወች፣ ኢምፔሪያሊዝም፣ ወታደራዊ አገዛዝ፣ የዘር አገዛዝ፣ የዲሞክራሲ አለመኖር፣ የመብት መጥፋት፣ እገሌ የሚባለው ጎሣ ጨቁዋኝ መሆን፣ እገሌ የሚባለው ጎሣ ጦረኛ መሆን፣ ወዘተረፈ" እያሉ ጽፈዋል። የሚደማመጥ የለም እንጅ የሚጻጻፍ ሞልቶ ነበር። በመጻጻፍ የተግባባ እስካሁን አላየንም። በመጻጻፍ መበሻሸቅ ግን በየቀኑ የምናየው ትዕይንት ነው። ተጽፈው የምናነባቸው መፍትሄወችም "የትጥቅ ትግል ማድረግ፣ ተጨማሪ የሚወነጅሉ ጽሁፎችን መጻፍ፣ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ፣ ጉልበት ላላቸው መንግሥታት ማመልከቻ ማቅረብ፣ ወዘተረፈ" የሚሉ ናቸው። ሁሉም ተደረጉ፤ መልካም ቀን አልመጣም። በጦር ብልጫ ወይም በተቃውሞ ብዛት አንዱ አሽናፊ ከሆነ ሌላው ደግሞ ጠመንጃ አንስቶ የተዋጊነት ዙር ይደርሰዋል። ኢትዮጵያን ከጦር ሜዳ፣ ወይም ከሰላማዊ ሰልፍ መንበር፣ ወይም ከኃያላን መንግሥታት ችሮታ ለማግኜት መሞከር ሞኝነት ነው። መልካምዋ ኢትዮጵያ ከኃያላን መንግሥታት ጀርባ አልተደበቀችም። በጦርነትና በሰላማዊ ሰልፍ ማህደር ውስጥም አልተሸሸገችም። በክፉ ሥራችን ከኛ ጠፍታለች፤
እንድናገኛት ከእግዚአብሔር እጅ እንሻት

የእግዚአብሔር ፍርድ ሳይዉል ሳያድር የሚፈጸምባት ወይም የሚፈጸምላት ክፉ ሥራችን ያጠፋት ኢትዮጵያ በእግዚአብሔር የተለየች ሀገር መሆንዋን ያልተገነዘቡ መልሰው መላልሰው ቢያስተዉሉ መልካም ነው። እንደራስ መሆንን ትቶ ሌሎችን ለመምሰል መጣር ይህን ካለማስተዋል የመነጨ ፍላጎት ነው።         

ልጅ እያሱ በግርማዊነታቸው በአፄ ኃይለሥላሴ ትእዛዝ እስር ቤት እያሉ ጣሊያን ኢትዮጵያን መውረር ጀመረ። ጣሊያን እየገሠገሠ ሲመጣ ግርማዊነታቸው ወደዉጭ አገር ገለል ብለው በውጭ ለመታገል ከመውጣታቸው በፊት የልጅ እያሱን ሁኔታ በተመለከተ ከቅርብ አማካሪወቻቸው ጋር ተነጋገሩ። ጣሊያን ሲገባ ህዝብን ለማሳመንና የፖለቲካ መጠቀምያ ለማድረግ ልጅ እያሱን "ንግሥና የሚገባው ንጉሥ ይሄዉና" ብሎ ንጉሥ አድርጎ ያነግሣል የሚል ፍራቻ በንጉሡና በአማካሪወቻቸው አደረ። ይህ ከሚሆን ብንገንድለውስ ብለው ተማከሩ። አፄ ኃይለሥላሴም "ንስኃውን እንዴት እንችለዋለን?" ሲሉ የነብስ አባታቸው አባ ሃና ጅማ "እንጾመዋለን" አሉዋቸው። ልጅ እያሱ በእስር ቤት ውስጥ ስንቅ ከሚያቀብላቸው ሠራተኛ ጋር እያወሩ የሚገድሉዋቸው ሰወች ከነሱም አንዱ የአባ ሀና ወንድም ኃይሌ ጅማ ሲመጡ ከሩቅ አዩና "ሊገድሉኝ እየመጡ ነው" ደህና ሰንብት ብለው ስንቅ አቀባያቸውን ተሰናበቱት። ከዚህ በሁዋላ የልጅ እያሱ አስከሬን የት እንደደረሰ አይታወቅም። [፩]  

ግርማዊ አፄ ኃይለሥላሴ በደርግ ትእዛዝ እስር ቤት እያሉ የደርግ አባሎች ምን እናድርጋቸው እያሉ መከሩ። እሳቸው በህይወት እያሉ የኢትዮጵያ ህዝብ እንዴት ሊገዛልን ይችላል ብለው አዲሶቹ የሀገር መሪ ወጣት የጦር መኮንኖች ንጉሡ በእስር ቤት እንዳሉ ለመግደል አቀዱ። አፄ ኃይለሥላሴ በእስር ቤት ዉስጥ ስንቅ ክሚያቀብላቸው ሠራተኛ ጋር ሲያወሩ ዛሬ ከእርስዎ ጋር እንደማላድር ተነግሮኛል አላቸው። አዝነው አለቀሱ። ወዲያውም የሚገድሉዋቸው መኮንኖች ሲመጡ ከሩቅ አዩና አወቁ። ከዚህ በሁዋላ አስከሬናቸው የት እንደደረሰ ሳይታወቅ ከደርግ መውደቅ በሁዋላ አጥንታቸው ተፈልጎ ተቀበረ ተባለ። የነብስ አባታቸው አባ ሃናም በሰው እጅ ነበር የጠፉት።  [፪]

ጣልያን ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ግርማዊ አፄ ኃይለስላሴ ሊግ ኦፍ ኔሽንስ በተባለው የዓለም መንግሥታት ማህበር ስብሰባ "ጉልበተኛ ጉልበት የሌለውን በግፍ ሲያጠቃ ዝም ብላችሁ አትዩ፤ ነገ በናንተ ላይ ይደርሳልና" ብለው ጣልያን ከኢትዮጵያ ለቆ እንዲወጣ አቤቱታ አሰሙ። በጉባኤው የነበሩ የአውሮጳ ሃያላን መንግሥታት ተሳለቁባቸው።

ጣሊያን በኢትዮጵያ ዉሎ ሳያድር የጣሊያን ጉዋደኛ የሆነው ጀርመን የአውሮጳን ኃያላን በእግሩ እየረገጠ ማንበርከክ ጀመረ። አንድ ባንድ አውሮጳን ይወርም ጀመረ። በአፄ ኃይለሥላሴ አቤቱታ የተሳለቁት መንግሥታት በኢትዮጵያ ላይ የደረሰው በራሳቸው ላይ እየደረሰ በመምጣቱ ተደናገጡ። ከኢትዮጵያ ጎን በወታደርነት ተሰልፈው ጣልያንን እስኪአስወጡ ድረስ በኢትዮጵያ ላይ መሳለቃቸውን ረገሙ። የእግዚአብሔር ፍርድ እንዲህ ነው።

የጣልያኑ መሪ ቤኒቶ ሙሶሎኒ ኢትዮጵያን በወረሩበት ጊዜ ብዙ ግፎችን ሠርተው፣ አሰቃቂ ፍርዶችንም ፈርደው ነበረ። መነኮሳትን በየገዳሙ በጥይት ጨፍጭፈው ገድለዋል፤ በመርዝ ጋዝና በኬሚካል መሣሪያወች የኢትዮጵያን ህዝብ ጨፍጭፈዋል፤ አርበኞችን ከአውሮፕላን ከሰማይ ወደምድር ዘቅዝቀው ወርውረዋል። ቤኒቶ ሙሶሎኒ ከሠሩዋቸው ግፎች ዉስጥ አንዱ የእግዚአብሔርን ሰው አቡነ ጴጥሮስን አዲስ አበባ ላይ አስረው በተጣደፈ ችሎት የሞት ፍርድ አስፈርደው በጥይት አስደብድበው መግደላቸው ነው።

የጣሊያን ጦር ከኢትዮጵያ ከተባረረ በሁዋላ ትልቁ የጣሊያን ጠቅላይ ሚንስትር ቤኒቶ ሙሶሎኒ ከአገራቸው ሊወጡ ሲገሠግሱ የጣልያን ሶሻሊስቶች ይዘው በተጣደፈ ችሎት የሞት ፍርድ በየኑባቸው። በፍርዱ መሠረት ወዲያውኑ ቤኒቶ ሙሶሎኒ እንደ አቡነ ጴጥሮስ በጥይት ተደብድበው ተገደሉ። በሚላን ከተማ ሬሳቸው ተዘቅዝቆ ተሰቀለ። ከዚህ በኢትዮጵያ ላይ ከተፈፀመ የግፍ ወረራ ዘመን በሁዋላም ጣልያን ከአውሮጳ ጅራቶች ዉስጥ አንድዋ ሆና ቀረች።

የዛሬ አራት መቶ ሃምሳ አመት አካባቢ ኦስማኒየ ወይም ኦቶማን ኢምፓየር የተባለ ማእከሉ ቱርክ የሆነ በዘመኑ በዓለም ላይ አቻ የሌለው መንግሥት የውስጥ አመፀኛን በማስታጠቅ እንዲሁም ወታደሮቹን በአካል መሣሪያ አስይዞ ክርስትናን ከኢትዮጵያ ለማጥፋት ወደኢትዮጵያ መጣ። ትልቅ ጥፋትንም አደረሰ። አብያተክርስቲያናት ተቃጠሉ፣ መነኮሳት ታረዱ።

ለሁለት መቶ አምሳ አመታት በኃያልነት በማንም ሳይደፈር ከቆየ በሁዋላ የኦቶማን ኢምፓየር በኢትዮጵያ ላይ ጥፋትን አድርሶ ብዙ ሳይቆይ ለመጀመሪያ ጊዜ በላፔንቶ ጦርነት ተሽንፎ የሜዲትራንያንን ባህር መቆጣጠር አቃተው። ቀስ በቀስም እንደጉም በኖ ጠፋ። 

በተለይ የኦቶማን ኢምፓየር ቅሬታወች ነን የሚሉ መንግሥታት ባለፉት አምሳ አመታት ኢትዮጵያን በጦርነት አደህይተው፣ ወደቦችዋን ነጥቀው፣ የንግድ በርዋን ዘግተውና ህዝቦችዋን አናክሰው ህልውናዋን በማጥፋት ሥራ ላይ ተሰማርተው የሚፈልጉትን እስከሚችሉት አከናወኑ። እነዚህ መንግሥታት እንደአባቶቻቸው ኦቶማኖች የውስጥ አመፀኛን በማስታጠቅ ይህ ነው የማይባል ጥፋትን አድርሰዋል። አንድ ጊዜ መንፈሰ መራራ እንዲሆኑ በውጭ አገር ሰወች የተሰበኩ ኡስማን ሳልህ ሳቤ የተባሉ ሰዉየ ኢትዮጵያውያን ሱዳን አገር በሚገኝ የመዳህኒዓለም ቤተክርስትያን አብረው በመፀለይ ላይ እንዳሉ "ኤርትራውያን የተለያችሁ ናችሁ፤ ለናንተ እኔ ቤተክርስቲያን ለብቻችሁ እገዛላችሁዋለሁ" በማለት ከነዚህ መንግሥታት ባገኙት ገንዘብ ህንፃ ገዝተው የኤርትራውያን ሚካኤል ቤተክርስቲያን ብለው ሰየሙና ኢትዮጵያውያንን ከፋፈሉዋቸው። [፫] በተለይ የባዝ ፓርቲ ተብሎ የሚጠራው የኢራቅ ፓርቲ ቀይ ባህርን አረቦች ብቻ ይቆጣጠሩት ዘንድ ኤርትራ ከኢትዮጵያ እንድትገነጠልና ኢትዮጵያ ተቆራርጣ የንግድ በር እንድታጣ ለአረቦች ጥሪ አደረገ። የነዚህ መንግሥታትም ገንዘብ  እንደ ጥፋት ልኡክ ሆኖ ኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ ደም ፈሰሰ።

እነሆ ለነዚህ መንግሥታት በጦርነት አደህይቶ፣ የንግድ በራቸውን ተቆጣጥሮ፣ ህዝባቸውን አናክሶ የሚፈልገውን የሚያከናውን ኃይለኛና የሚረግጥ የበላይ ሰጣቸው። አንዳቸው ብቻ አይደሉም - ሁሉም የሠሩትን ግፍ የሚያህል ፅዋ እየተጎነጩ ነው። ማን ያውቃል - እስላም ያልሆነው ኃይለኛው መንግሥት በመካከላቸው ባስቀመጠው ወኪል አማካኝነት ለአንዱ ዘር የተለየ መስጊድ ይገዛለት ይሆናል። 

አምባሳደሮችዋን ክንፍ ባላቸው መርከቦች በዓለም ላይ የምታሰማራው የአሜሪካ ልኡክ የሆኑ የመጣሁት አረቦች ኤርትራን ገንጥለው የራሳቸው ለማድረግ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ ለማጨናገፍ ነው እያሉ ከኤርትራው ጠቅላይ ገዥ ጋር በመሆን ከአቶ ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ለመገናኘት በቀጠሮ ወደቃኘው ሻለቃ አመሩ። ኤርትራን ከኢትዮጵያ ለመገንጠል ቢታገሉ እንደማይቃወሙ እንደሚረዱዋቸውም ከጠቅላይ ገዢው ዘወር አርገው ለአቶ ኢሳያስ አፈወርቂ ማበረታቻ ሰጡዋቸው። [፬] ከዚህ ጊዜ በሁዋላ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ትገነጠል ዘንድ የኢትዮጵያን ሀገርነትና ኃይማኖትዋን የሚያጥላሉ ሚሽነሪወችን በማሰማራት፣ እንዲሁም ከሰላይ እስከ ደላይ፤ ከጋዜጠኛ እስከ ጎብኝ፣ ከስነፅሁፍ እርዳታ እስከገንዘብ ድረስ በማቅረብ ኢትዮጵያን አዳከሙ። ኢትዮጵያ ትከፋፈል ዘንድ፣ የንግድ በርም ታጣ ዘንድ ከአረቦች ጋር አላማቸው አንድ ሆነ። ሶስት መቶ ስልሳ አንድ ወደቦች ያላት ታላቁዋ አገር አሜሪካ አንድ ብቻ ያላትን የተራበችዉን፣ የደሃዋን አገር በር ለመንሳት አምባሳደርዋን ላከች። ፈፀመችም። ኢትዮጵያን ለመክፈል፣ የንግድ በርዋንም ለመዝጋት በሌላ አገር ላይ ተደርጎ የማይታወቅ ኢትዮጵያን ያለ በር ማስቀረት የሚያስችል የመንግሥታት ማህበር ድንጋጌ በልዩ ዘዴ ተነደፈ። ተጨበጨበ። ተፈጸመም።

ለምልክት እንዲሆን በኢትዮጵያ አዲስ አመት እለተ ቀን፣ ኢትዮጵያን ለማጎሳቆል አላማ  ከተወዳጀቻቸው ወገኖች የተሰነዘረ ጥቃት በአሜሪካ ላይ ደረሰ። በስማይም በባህርም ብዙ ሺ መንገድ ያላት አገር በሮችዋ እንደ አንድ በር ሆኑና ሰማዩም ባህሩም የስጋት ሆነባት። በአንድ እለተ ቀን የተፈፀመ ጥቃት አጥቂወቹም ተጠቂወቹም በማያውቁት መንገድ የእያንዳንዱን ሰው ኑሮ ዳሰሰ፤ አቃወሰ። የተጠቂዋ ንግድ በጥቃቱ ተጎዳ፣ ደስታዋም አነሰ። በሰማይዎችዋና በባህሮችዋ ያለባትን ስጋት ለመሸፈን በየቀኑ ቁጥር ስፍር የሌለው ኃብትዋን በመድፋት ላይ ትገኛለች።  

ኢትዮጵያን የበደለ ይበደላል። እነ ታላቅዋ ብሪታንያ፣ እነ ዩ ኤስ ኤስ አር፣ እነ ፖርቱጋል ወዘተረፈ የሚመጣጠነውን ዋጋቸውን አግኝተዋል። አንድ የእግዚአብሔር ሰው አንድ ጊዜ "ኢትዮጵያን አይነኩ፤ ቢነኩ ያድርዋል ሲታወኩ" ብለው የተናገሩት ያለምክንያት አይደለም። ትናንትናም ዛሬም ነገም አይቀየርም - የነካት ይነካል። በኢትዮጵያውያን የተሠራ ኃጢአትም ወዲያዉኑ ፍርድ ያገኛል። አሁን እየተጎነጨን ያለነው ፅዋ ለሠራነው ኃጢአት የሚመጣጠነውን ነው። ፍቅር የለን፤ እንዴት አንድ እንሁን? ምቀኝነት ምግባራችን፤ እንዴት እንበልጽግ? የውጭ የምናይ፤ እንዴት የራሳችን ይክበር? አጉል ምግባራችን ያጠፋት መልካምዋ ኢትዮጵያ በእግዚአብሔር እጅ ተይዛለች። የምትገኘው በሱ ነውና እሱን እንፈልገው።
እንድናገኘውም ከፍቅር ማህበር እንጥራው
 
እገሌ እንዲህ አድርጎ ስለበደለን እንዲህ ሆነናል እያልን ከዘመን ዘመን የተለያዩ ሰወችን እያማረርን፣ ተጠያቂወቹ እነሱ ናቸው እያልን እንኑር ወይ? ውድቀታችን ያመካኘንባቸው ሰወች ከየት መጡ? የውድቀት ተጠያቂወች የሚቀያየሩ ከሆነስ ውድቀት እንዴት ሊቆም ይችላል? ጨቁዋኞችስ ለምን መጡ? ሁከተኞች ለምን መጡ? አገር መገንጠል የሚፈልጉ ለምን መጡ? ያልተሰጣቸውን የሚነጥቁ ለምን መጡ? ዘጠና ስምንት ከመቶ በላይ የሚሆነው ኢትዮጵያዊ በእግዚአብሔር ያምናል። ከግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለስላሴ የንግሥና ዘመን ማለፍ በሁዋላ የተሰየሙት እግዚአብሔር የለም የሚሉ ሁለት መንግሥቶች በእግዚአብሔር ከሚያምን ህዝበ-ውቅያኖስ መካከል ወጥተው እንዴት መሪ ሊሆኑ ቻሉ? ልብ ላደረገው መልሱ እራሱ ከጥያቄው ዉስጥ ይገኛል።      

እግዚአብሔር ጭቆና አይወድም። ወንድሙን እና እህቱን የሚወድ ወንድሙንና እህቱን አይጨቁንም። ጉዋደኛዉን የሚወድ ጉዋደኛውን አያጭበረብርም። የተጨቆነ ወንድም ለመውደድ ይቸገራል። የተታለለ ባልንጀራ ግዋደኝነትን አይሻም። ክፉ አመልን እንደያዝን የምንገነባው ይፈርሳል። የምናደርገው ነገር ሁሉ ዉኃ ቢወግጡት ይሆናል። ባለዘመን ቢገነባ የሚከተለው ያፈርሰዋል። ዘንድሮ የተወደሰው ከርሞ ይረክሳል። ኢትዮጵያን ከክፉ ቀን ለማዳን የሚያስፈልገን አንድ ነገር ብቻ ነው። እሱም ፍቅር ነው። ፍቅር ካለ ጭቆና የለም። ፍቅር ካለ ማጭበርበር የለም። ፍቅር ካለ አመፅ የለም። በፍቅር የተገነባ በበቀል አይፈርስም። ፍቅር ካለ እንገነጣጠል የሚል ዛቻ የለም። ፍቅር ካለ ስብሰባውም ሆነ ስነፅሁፉ ስለ መገንባት ጉዳይ እንጂ ስለ ጦርነት ጉዳይ አይሆንም። እግዚአብሔር ፍቅር ነውና ስንፋቀር እግዚአብሔርን እናገኘዋለን። እግዚአብሔርም መዳብ መስሎን የነበረው እኛነታችን አይናችን ገልጦ ወርቅ መሆኑን ያሳየናል። የምንበላውና የምንጠጣው የሌለ የመሰለው ልቦናችንን አንቅቶ በኤደን ገነት ውስጥ እንደምንኖር ይስመለክተናል። የውጩ የሚያስጎመጅ የመሰለው አዕምሮአችንን ብሩህ አድርጎ በእጃችን ያለው እንቁ መሆኑን ያሳየናል። ስለዚህ የፍቅርን ሥራ እንጀምር።

**********************************************************************************
፩ ይህን ያሪክ ያጫወቱኝ በጊዜው ጉዳዩን የሚያውቁ አረጋዊ ናቸው።
፪ ይህን ያሪክ ያጫወቱኝ በጊዜው ጉዳዩን የሚያውቁ አረጋዊ ናቸው።
፫ ይህን ታሪክ ያጫወቱኝ በሱዳን አገር በስደት የኖሩና ጉዳዪን በአይናቸው ያዩ የባህረ ነጋሽ ተወላጅ ናቸው። 
፬ ሲ አይ ኤ በአፍሪካ፣ በአለሜ እሸቴ፣ ፲፱፻፺፬ ዓ.ም.

****************************************
 ምንጭ:--http://www.oftsion.org/SeektheLord.html

“የህይወት ጥቅሙ ምንድነው?”

 መቼም የማይሞት ሰው የለም
******************************

“በመልካም ስራው ሲታወስ ይኖራል” እንዳትሉ። ከሞተ በኋላ ታሪኩ ቢነገር መቼ ይሰማና!
“ስምና ስራ ከመቃብር በላይ ነው” እንዳትሉ። ከሞተ በኋላ አድናቆትና ክብር ምን ሊረባው!
“ድንቅ ስኬታቸው ዘላለማዊ ናቸው” አትበሉ። ከሞት በኋላ ምንም ነገር ትርጉም የለውም!
ጀግኖች፤ በህይወት እያሉ ነው በመልካም ስራና በድንቅ ስኬት ዘላለማዊነትን ያጣጣሙት!
የድፍረት አባባል እንዳይመስላችሁ። ርዕሱ ላይ፤ “የማይሞት ሰው የለም” ብዬ ስፅፍ፤ ... ዝግንን ብሎኛል። የተለመደ አባባል ስለሆነ፤ ብዙውን ጊዜ ያን ያህልም ስሜት ላይሰጣችሁ ይችላል። “ህይወት አላፊ ነው” ይባላል - እንደ ዋዛ። አንዳንዴ ግን፤ “የማይሞት ሰው የለም” ብላችሁ ስትናገሩ ወይም ስትሰሙ፤ ...የምር ውስጣችሁ ድረስ ጠልቆ ይሰማችኋል - ሰውነትን የሚያስፍቅ ሸካራ ስሜት። ሳይበርዳችሁ... ቆዳችሁ ተሸማቅቆ ፀጉራችሁ ይቆማል።
እስከ ዛሬ ያካበታችሁት እውቀትና ችሎታ፤ የሰራችሁትና ያፈራችሁት ነገር ሁሉ፤ ለወደፊት ያሰባችሁትና ያቀዳችሁት ሁሉ፤ የምታፈቅሩትና የምትሳሱለት፤ የሚያስደስታችሁና የሚያጓጓችሁ ነገር ሁሉ... ድንገት ትርጉም ሲያጣ ይታያችሁ። የምን ማየት! ከሞት በኋላ አንድ አፍታ ለማየትም እንኳ እድል የለም። ዛሬ አለሁ፤ ነገ የለሁም። ... አለቀ፤ እስከ መቼውም የለሁም። ለሞተ ሰው፤ “ከዚያ በኋላ....” የሚባል ነገር የለም። “ከዚያ በፊት... ከዚያ በኋላ” ብሎ ሊያስብና ሊናገር አይችልም። ጨርሶ የለማ። በቃ፤  ብን ብሎ ድንገት ጥፍት... ባዶ... ። ታዲያ የህይወት ትርጉም ምንድነው?
ሰው ቢሞትም፤ “ከዚያ በኋላ...” የሚባል ነገር ይኖረዋል ብሎ መሟገት እንደሚቻል አውቃለሁ። አሁን ግን፤ ጠያቂውና ተጠያቂው እኔ ራሴ ስለሆንኩ፤ መከራከሪያና ማሳመኛ አይሆነኝም። ከሞት በኋላ ህይወት እንዳለ ማየትና ማረጋገጥ ሳይቻል፤ ከራስ ጋር ተከራክሮ ማሳመን ከባድ ነው። ለነገሩ፤ ከዚህኛው ዓለም ባሻገር፤ ሌላ “የወዲያኛው ዓለም” ቢኖር እንኳ፤ እንዴት ማፅናኛ ሊሆን እንደሚችል አይገባኝም።
የሞተ ሰው፤ ወደ ወዲያኛው አለም ይሄዳል እንበል። ግን፤ ይሄኛውን አለም ተመልሶ ማየት አይችልም። የሚወደውን ስራ ተመልሶ ሊሰራ አይችልም። የሚወደውን ምግብ መቅመስ፣ ከሚያፈቅራቸው ሰዎች አጠገብ መሆንና ማነጋገር አይችልም። ምንም ማድረግ አይችልም። ሰዎችም ምንም አያደርጉለትም። ቢበዛ ቢበዛ፤ የትዝታቸው ቅንጣት ውስጥ ታሪኩን ያስታውሱ ይሆናል። እሱ ግን  ...የለም፤ ከእንግዲህ አይኖርም። ታዲያ፤ በህይወት ዘመኑ ውስጥ፤ እንዲያ ብዙ በሃሳብ መብሰልሰሉና ለነገ ማቀዱ፤ ማውጣትና ማውረዱ፣ ለስራ መድከሙና ለውጤት መጣጣሩ ምን ትርጉም አለው? የህይወት ፋይዳስ ምንድነው?
ዘመናዊ ማፅናኛዎቻችንን ሳላስባቸው የቀረሁ እንዳይመስላችሁ። “ሰው ይሞታል፤ ስራው ግን ህያው ነው” እንደሚባል አውቃለሁ። “ስምና ስራ ከመቃብር በላይ ናቸው” ሲባልም እሰማለሁ። “በአካል ብትለየንም በመንፈስ ከኛ ጋር ነህ” ይባላል። “ሰው በመልካም ስራውና በድንቅ ስኬቱ ህያው ይሆናል” ... ይህንንም ሰምቻለሁ፤ እንዲያውም እኔ ራሴ ብዙ ጊዜ የምለው ነገር ነው። “በሰራኸው መልካም ስራ ዘላለም ህያው ትሆናለህ፤ ዘላለም በክብር ታሪክህ ሲታወስ ይኖራል” ይባላል። ...አባባሎቹ የሆነ ደስ የሚል ነገር አላቸው። እኔም አባባሎቹን እወዳቸዋለሁ።
ነገር ግን፤ እንዲህ አይነት ሺህ እና ሺህ አባባሎች ተሰብስበው ቢደመሩ፤ ለሟች ነፍስ ሊዘሩና ህይወትን ሊመልሱ አይችሉም። በህይወት ያሉ ሰዎች፤ እነዚህን አባባሎች እንደመፅናኛ ሊጠቀሙባቸው ይችላሉ። ምናልባትም መንፈሳቸው ይነቃቃ ይሆናል - በህይወት ካሉና አባባሎቹን ከሰሙ። በህይወት ለሌሉና መስማት ለማይችሉ ግን፤ እነዚያ እልፍ አባባሎች በሙሉ ትርጉም የላቸውም። ከሞተ በኋላ፤ “ታሪኬ እንዴት ይወራ ይሆን?” ብሎ የሚያስብ ሰው የለም። አላሰበም ወይም አያስብም ማለቴ አይደለም። ለማሰብ፤ በቅድሚያ በህይወት መኖር አለበት። ከሞት በኋላ ግን፤ ... በቃ ...የለም።
ከመኖር ወደ አለመኖር መሻገር... ከዚያ በኋላ ምንም የለም። ባዶ ነው። ምን ያህል ሰው በስራዬ ያደንቀኝ ይሆን? ስንቱስ በሞቴ ያዝንልኛል? የቀብሬ አከባበር እንዴት ይሆን? የጀመርኩትና የገነባሁት ቢፈርስስ? ያቀድኩትና የተለምኩትስ ይሳካ ይሆን? ታሪኬ ዘላለም ይቆያል ወይስ እረሳ ይሆን?... ከሞት በኋላ እነዚህ ሁሉ ጥያቄዎች ፋይዳ የላቸውም። ለማን ሊፈይዱ! ለማን ሊጠቅሙ! ከሌለህ የለህም። ሁሉም ነገር አብቅቷል። ታዲያ የህይወት ፋይዳው ምንድነው? የመንግስቱ ለማ ግጥም አይመጣባችሁም? (ስንኞቹ ውስጥ “ት” ጠበቅ ተደርጋ ስትነበብ ነው ቤት የሚመታው)





ለምንድነው አልኩኝ
በምን ምክንያት
ህፃን መወለዱ
አርጅቶ ሊሞት...






በጨላለመ ሃሳብና ስሜት የጀመርኩት ፅሁፍ፤ ድንገት የመጣ እንዳልሆነ መገመታችሁ አይቀርም። ከጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ዜና እረፍት ጋር ብዙ ሰዎች ብዙ ነገር አስበዋል። ስለ አገሪቱ የወደፊት እጣ ፈንታ አውጠንጥነዋል። ፖለቲካውና የስልጣን ሽግግሩ አሳስቧቸዋል። የኢኮኖሚና የኑሮ ሁኔታ እንዴት ይቀጥል ይሆን ብለው አሰላስለዋል ... በአመዛኙም ስጋትና ጥርጣሬ በተሞላበት መንፈስ። ለየት የሚል መንፈስ የሚጫጫናቸው ግን፤ ስለ ህይወትና ስለ ሞት ሲያስቡ ነው - “የህይወት ፋይዳ ምንድነው?” ከሚል ጥያቄ ጋር ተጭኖ የሚመጣ የጨላለመ መንፈስ።
በእርግጥ፤ ይሄ ጨለማ መንፈስ፤ ከሃዘን ስሜት ጋር ስለሚደባለቅና ስለሚቀየጥ፤ ሁለቱን በግልፅ ለይቶ ለማውጣትና ለማየት ያስቸግራል። ግን፤ ጨለማው መንፈስ ከሃዘን ስሜት ይለያል፤ ይብሳል። የሃዘን ስሜት፤ “አንዳች ነገር ማጣት”ን የሚያመለክት ነው - ተፈጥሯዊና ተገቢ የሆነ ስሜት። “የህይወት ፋይዳ ምንድነው? ምን ትርጉም አለው?” ከሚለው ጥያቄ ጋር አብሮ የሚከሰተው ጨለማ መንፈስ ግን፤ “ራስን ከማጣት” ስሜት ጋር የተያያዘ ነው - ከተሳሳተ አስተሳሰብ የሚመነጭና ተገቢ ያልሆነ ጨለማ መንፈስ።
ማጣትና ማዘን - ከትንሽ እስከ ትልቅ
አቤት የሃዘን አይነትና መጠን አበዛዙ! ለነገሩ የደስታ አይነትና መጠንም እጅግ ብዙ ነው። አይነታቸው ይብዛ እንጂ ከሁለት ምንጮች የሚፈልቁ ናቸው። ደስታ የሚመነጨው በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ፤ ከ”ስኬት” ነው። “ማጣት” ደግሞ ሃዘንን ያስከትላል። ደስታና ሃዘን የእለት ተእለት ህይወታችን ቢሆኑም፤ ከስኬትና ከእጦት የሚመነጩ መሆናቸው በግልፅ ይታየናል ማለት አይደለም። ባይታየን ደግሞ አይገርምም። የብዙዎቻችን ህይወት በአርቴፊሻል “ደስታ እና ሃዘን” ሲበረዝ ውሎ የሚያድር ነውና። እንዴት በሉ።

የውሸት “ደስታ”ን እያውለበለብን መፈንጠዝ ያምረናል - ያልደረስንበትን ስኬት እንዳገኘነው እየቆጠርን። ወይም አላስፈላጊ “ሃዘን” ተከናንበን ትካዜ ውስጥ እንነከራለን - አላግባብ በጥፋተኝነት ስሜት ራሳችንን እየወቀስን። በመጠጥ ሞቅታ የሚገኘው ደስታ ከየትም የሚመጣ አይደለም። ሰዎች ሞቅ ሲላቸው ሃብታም ወይም ጀግና፤ አዋቂ ወይም ትልቅ የሆኑ ሲመስላቸውኮ፡፡ “ስኬታማ ነኝ” ብለው አሰቡ ማለት ነው። “ስኬት” ደግሞ ደስታን ይፈጥራል - ጊዜያዊ አርቴፊሻል ደስታ። የአስመሳዮች ደስታም ተመሳሳይ ነው። ባልሰሩትና ባልፈጠሩት ስኬት፤ በአስመሳይነታቸው የሰው አድናቆትና ሙገሳ የሚጎርፍላቸው ሰዎች በደስታ የሚሆኑትን ሊያጡ ይችላሉ። በሙገሳ ሲሰክሩ፤ ስኬታማ የሆኑ ይመስላቸውና፤ ደስታ ይሰማቸዋል።
ችግሩ፤ ማታ ሰው ሁሉ ተኝቶ ሙገሳው ሲቋረጥ ወይም በማግስቱ ሞቅታው ሲበርድ፤ “ስኬታማ ነኝ” የሚለው የስካር ሃሳብም አብሮ ይጠፋል፤ “የውሸት ደስታውም” እንዲሁ። በእውነተኛ ስኬት ላይ የተመሰረተ እውነተኛ ደስታ ግን፤ በአንድ ሌሊት እንቅልፍና በአድናቂ እጦት በኖ አይጠፋም። የሆነ ሆኖ፤ ማንኛውም የደስታ አይነት፤ የውሸትም ይሁን የእውነት ደስታ፤ ዞሮ ዞሮ ከ”ስኬት” ጋር የተቆራኘ ነው (የእውነትና የውሸት ስኬት)።
የሃዘን ምንጭም፤ (ሃዘኑ ተገቢም ይሁን አላስፈላጊ)፤ ከ”ማጣት” ጋር የተያያዘ ነው - (የእውነትና የውሸት እጦት)። ያስቀመጥነውን ውድ እቃ ፈልገን ካላገኘነው፤ የጠፋና ያጣነው እየመሰለን እናዝናለን። ግን ጊዜያዊ ስለሆነ ብዙም አይጎዳም። መጥፎነቱ እጅግ ጎጂ የሆኑ አላስፈላጊ ሃዘኖችም አሉ። ከፍተኛ የፈተና ውጤት በማስመዝገቡ እየተደሰተ፤ ነገር ግን ከጓደኞቹ በመብለጡ የጥፋተኝነት ስሜት የሚፈጠርበት ተማሪ አለ - ጓደኝነታቸውን የሚያጣ እየመሰለው። በቢዝነስ ስራው ስኬታማ እየሆነ ደስታ ቢያገኝም፤ ገዳም የመግባት ፍላጎት በማጣቱ ራሱን እንደጥፋተኛ የሚቆጥርም ጥቂት አይደለም። እነዚህ አላስፈላጊ ሃዘኖች ናቸው።
ከ”ማጣት” (ከመጎዳት) የሚመነጩ እውነተኛ ሃዘኖችም ቢሆኑ አስፈላጊ ናቸው ማለቴ አይደለም። ግን ተፈጥሯዊ ናቸው። አንድን ነገር መውደድና ማክበር ማለት፤ ያስደስትሃል ማለት ነው፤ ስታጣው ደግሞ ያሳዝንሃል... የግድ ነው። ሁሉም ሃዘኖች ከማጣት የሚመነጩ ቢሆንም፤ ስፋትና ክብደታቸው ግን... የትና የት! የሚያኮማትር፣ እየቆየ የሚያስደነግጥና ግራ የሚያጋባ ሃዘን እንዳለ ሁሉ፤ ከአፍታ ብልጭታ የማያልፍ ሃዘንም ይኖራል።

ሃዘን የሚለውን ቃል በየጊዜው ምን ያህል እንደምንጠቀምበት አስቡት። ልብሷን ጭቃ ሲነካት አሳዘነችኝ ይላል። አዳልጦት ስለወደቀ አሳዘነኝ ትላለች። ካልተጎዳ ተመልሶ ይነሳል። ጭቃ የነካው ልብስም፤ ታጥቦ ይነፃል። ያጣነውን ነገር ቶሎ መልሰን የምናገኘው ከሆነ፤ ለሃዘን ፊት አንሰጠውም - ከወደቅንበት እንነሳለን፤ የጨቀየውን እናጥባለን። ግብዣ ጠርተውት ሳይመጣ በመቅረቱ፤ ብርጭቆው ስለተሰበረ፣ የልጅነቱ ፎቶ ስለተቃጠለ፣ የቤቱ ጣሪያ ስለተገነጠለ፣ በፈተና የማለፊያ ውጤት ስላጣ፣ የአሜሪካ ቪዛ ስለተከለከለ፣ ገንዘብ ከቦርሳው ስለተሰረቀ.... ያዝናል። ከፍቅረኛው ጋር ስለተጣላ፣ የሚወደው ሰው ስለደኸየ፣ የራሱ ንብረት በጎርፍ ስለተወሰደ፣ ጓደኛው በመኪና ስለተገጨ፣ የራሱ አካል በአደጋ ስለጎደለ፣ የሚያደንቀው ሰው ስለታመመ ... በጣም ያዝናል። የሚያከብረው ሰው ስለሞተ... እጅግ አዝኖ ያለቅሳል።
ደረጃቸው የሰማይና የምድር ያህል ቢራራቅም፤ ሁሉም አይነት ሃዘኖች፤ ኮምጣጣውም ሆነ መራራው ሃዘን ... ከ”ማጣት” የሚመነጩ ናቸው። አንዳንዶቹ ሃዘኖች እጅግ መራራ የማይሆኑት፤ ያጣነውን ነገር መልሰን ልናገኘው ስለምንችል ነው። ጊዜና ጥረት ያስፈልገው ይሆናል እንጂ፤ በተቃጠለብን ንብረት ምትክ ሌላ ንብረት የማፍራት እድል ይኖረናል። የለመድነው ወይም የምንወደው፤ የምናውቀው ወይም የምናከብረው ሰው ሲሞት ግን... መልሰን ልናገኘው አንችልም። ትዝታው ብቻ ነው የሚቀረን። የድሮውን ከማስታወስ በስተቀር፤ የድሮው ህይወት ተመልሶ እውን አይሆንም።
የሞት ሃዘን እጅግ መራራ ነው። በተለይ ከእለት ተእለት ህይወታችን ጋር የዘወትር ወይም የቅርብ ትስስር ያለው ሰው ሲሞት፤ ከሃዘኑ በተጨማሪ እየቆየ ድንግጥ ድንግጥ ያሰኛል። ቤት ስንገባና ስንወጣ፤ ድንገት እንድንገጣጠምና ድምፁን እንድንሰማ እንጠብቃለን። በየእለቱ የለመድነውና እንደ ቋሚ የተፈጥሮ ኡደት የምንቆጥረው ነገር ነዋ። ከብዙ ሃሳቦቻችንና ተግባራችን ጋር የተሳሰረ ነዋ። እናም፤ እንደለመድነው እንጠብቃለን።
ግን፤ ከእንግዲህ በአካል አናየውም፤ ድምፁንም አንሰማውም። ከእንግዲህ ጨርሶ የማይሆንና የማይቻል ነገር መሆኑ ብልጭ ሲልብን ድንግጥ እንላለን። ጭራሽ፤ በመጀመሪያዎቹ ቀናት ሃዘናችን እየበረታ ይሄዳል - በሞት ያጣነውን ሰው መልሰን ልናገኘው እንደማንችል በደንብ እየገባን ይመጣል። ከዘወትር የእለት ተእለት ልምዳችን ጋር የማይገጥም እውነታ ተፈጥሯል። ከዚህ እውነታ ጋር ስንፋጠጥ ድንግጥ እንላለን።
ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ በቲቪ ሲናገሩ ማየት ምን ያህል ከህይወታችን ጋር እንደተሳሰረ አስቡት። አሁንም ድንገት ቲቪ ከፍተን ስንመለከት... የጠ/ሚ መለስ ንግግር ስናይ... የምናውቀውና የለመድነው ነገር ነው። ... ግን ወዲያው ድንግጥ እንላለን። ለካ፤ ከእንግዲህ በጭራሽ ፓርላማ ውስጥ ንግግር ሲያደርጉ በቲቪ መከታተል አንችልም፤ ጨርሶ ሊሆን የማይችል ነገር ነው። ... ለወትሮው እንደ ነባር ስንቆጥረው የነበረ ነገር፤ አሁን ፈፅሞ የማይቻልና የማይሆን ነገር ... ከእንደዚህ አይነት ነገር ጋር ስንፋጠጥ ነው ድንጋጤ የተቀላቀለው ሃዘን የሚሰማን - ከ”ማጣት” የመነጨ ሃዘን።

“የህይወት ትርጉም - ዘላለማዊነትን ማጣጣም”
ሰውን በሞት ከማጣት የሚመነጭ የሃዘን ስሜት፤ ከሌሎቹ የሃዘን ስሜቶች ለየት ይላል። ብዙውን ጊዜ ሌላ ተጨማሪ ስሜት ይጭንብናል። “የማይሞት ሰው የለም” ከሚለው ሃሳብ ጋር፤ “ታድያ የህይወት ፋይዳው ምንድነው?” የሚል ጥያቄና ጨለማ መንፈስ ይፈታተነናል። ህይወት ትርጉም የሚያገኘው፤ ሞት የሚባል ነገር ከሌለ ነው ብለን ስለምናስብ ይሆን? ህይወትን ስለማናጣጥማትም ሊሆን ይችላል። እናም፤ ከሞት ባሻገር ከሞት ወዲያ ማዶ እንቃኛለን - የህይወትን ትርጉም ለማግኘት።
አንዳንዴ፤ በሌላ የወዲያኛው አለም፤ ሌላ የወዲያኛው ህይወት እንዳለ በማመን፤ ከጨለማው መንፈስ ለመገላገል እንጥራለን። ሌላ ጊዜ ደግሞ፤ “የሞተው ሰው፤ በስራው ህያውና ዘላለማዊ ሆኗል” በማለት ራሳችንን እናፅናናለን - የህይወት ትርጉም ታሪካዊ ስራ አከናውኖ ማለፍ እንደሆነ በማመን። ከሞት በኋላ ሌላ የወዲያኛው ህይወት ባይኖር እንኳ፤ “የታሪክ ህይወት” የሚባል ምናባዊ የህልውና አለም እንፈጥራለን - “በታሪክ ሲታወስ የሚኖር ሰው” እንላለን።
እንግዲህ፤ መሞት ማለት ዘላለማዊ ፍፃሜ መሆኑን ላለማመን ነው መፍጨርጨራችን። በዚህም፤ ጨለማውን መንፈስ አሽቀንጥረን የምንጥል ይመስለናል። መሞት ግን፤ ዘላለማዊ ፍፃሜ ነው (ቢያንስ ቢያንስ በዚህ በምናውቀው ዓለም ውስጥ)። እንዲያም ሆኖ፤ ከጨለማ መንፈስ ለማምለጥ ዘዴ መፈለጋችን አይቀርም። ሟቹ፤ ሃዘናችንንና አክብሮታችንን በማየት እንደሚደሰት አድርገን እናስባለን - ከሞተ በኋላም ህያው እንደሚሆን እያስመሰልን።
“ያሰብከውን እናሳካለን፤ ራዕይህን እውን እናደርጋለን” በማለት ቃል እንገባለታለን። ነገር ግን፤ ቃላችንን መስማት አይችልም። ሲያስብ የነበረውን ብናሳካና ባናሳካ፤ ይዞት የነበረውን ራዕይ ብንፈፅምና ባንፈፅም ለኛ ለራሳችን ካልሆነ በቀር፤ ለሟቹ ትርጉም አይኖረውም። ሊያስደስተውም ሆነ ሊያሳዝነው አይችልም። በህይወት የለማ።
እናም፤ ሃሳብና እቅዳችን፤ ጥረትና ተግባራችን ሁሉ የታለመው፤ ሟቹን ለማስደሰት ከሆነ፤ በከንቱ ደከምን - ቅንጣት አናስደስተውም። ሃዘንና ድንጋጤያችንን፤ ክብርና አድናቆታችንን መግለፃችን ለሟቹ ይጠቅመዋል ብለን ካመንን፤ በከንቱ ባከንን - ቅንጣት አንጠቅመውም። “ዘላለማዊ ነህ፤ ህያው ነህ፤ መንፈስህ ከኛው ጋር ነው” የምንለው፤ ለሟቹ በማሰብ ከሆነ፤ በከንቱ ለፋን - ቅንጣት እድሜ አንጨምርለትም።
ሃዘኑም ሆነ አክብሮቱ፤ ድንጋጤውም ሆነ አድናቆቱ፤ ትርጉም የሚኖረው፤ በህይወት ላሉ ሰዎች ነው። መልካም ስራንና ሰሪዎችን ማክበር፤ ስኬትንና ስኬታማዎችን ማድነቅ፤ እነዚህ ጀግኖች በህልውና ሲገኙ መደሰትና በህልፈታቸው ሲታጡ ማዘን... ይሄው ነው ቁምነገሩ። መልካም ስራንና ስኬታማዎችን ማድነቅ ለራስ ነው - ለራስ የስብእና ጤንነት።
ሟቾቹማ፤ ከማንም ምንም አይፈልጉም። ለሟቾች፤ ምንም ቢሆን ምንም ትርጉም የለውም - በህልውና የሉምና። “ህያው ናችሁ፤ ዘላለማዊ ናችሁ” ብንል ለነሱ ዋጋ የለውም። እኛ ስለተናገርን ወይም ስላልተናገርን አይደለም። አለማወቃችን እንጂ፤ ጀግኖችና የስኬት ሰዎች ዘላለማዊ ህልውናን የሚያጣጥሙት፤ ከሞት በኋላ ሳይሆን፤ በህይወት ዘመናቸው ውስጥ ነው - በእያንዳንዷ መልካም ስራና ድንቅ ስኬት ውስጥ ነው ዘላለማዊ ህልውናን የሚያጣጥሙት።
ጀግኖች፤ በአስተዋይነት ያመነጩት ሃሳባቸው ትክክለኛ መሆኑን ሲያውቁ፤ ትክክለኛነቱ መቼም የማይሻር ዘላለማዊ እንደሆነ ያውቃሉ፤ በዚህም ዘላለማዊነትን ያጣጥማሉ። አርስቶትል የሎጂክ መርሆችን ሲቀምር፤ የሃሳቦቹ ትክክለኛነት ዘላለማዊ መሆናቸውን በማወቅ ነው። አንድ ነገር፤ በአንድ ጊዜ ድንጋይ መሆንና ድንጋይ አለመሆን አይችልም።
ኮፐርኒከስና ጋሊልዮ፤ መሬት በፀሃይ ዙሪያ ትሽከረከራለች ሲሉ፤ ሃሳባቸው ትክክለኛነት ዘላለማዊ እንደሆነ ያውቃሉ። ያኔ ነው፤ ዘላለማዊ ህልውናን የሚያጣጥሙት። በህይወት ዘመናቸው ስለሚያጣጥሙትም፤ ከሞት በኋላ አሻግረው ሌላ የህይወት ትርጉም ለማግኘት በከንቱ መድከም አያስፈልጋቸውም። በእውነታ ላይ የተመሰረተች እያንዳንዷ እውቀት፤ በመረጃ ላይ የተመሰረተች እያንዳንዷ ሃሳብ፤ የዘላለማዊ ህልውና መስኮት ነች። በጀግኖች አርአያነት መንፈሳችንን እያነቃቃን፤ እውነታ ታማኝ በመሆንና በቅንነት በማሰብ ነው፤ በህይወት ዘመናችን ዘላለማዊ ህልውናን የምናጣጥመው።
ጀግኖች፤ በችግርና በእንቅፋት ብዛት ሳይበገሩ፤ ለአላማቸውና ለሃሳባቸው በፅናት በመቆም በድንቅ ብቃት መልካም ተግባር ይፈፅማሉ። ብቃትና ተግባራቸውም፤ ድንቅና ጠቃሚ መሆኑን ብቻ ሳይሆን፤ መቼም ለዘላለም እንደማይሻር ይገባቸዋል፤ እናም ዘላለማዊነትን ያጣጥማሉ። ተፈጥሮን መመርመርና ለእውቀት መትጋት፤ መማርና ማስተማር፤ ምርጥ የእህል ዘር መፍጠርና ወንዝ መገደብ፤ ማሽንና ቴሌፎን፣ ክትባትና መድሃኒት ለመስራት ሙከራና ጥናት ማካሄድ... እነዚህ ብቃትና ተግባሮቻቸው እጅግ ድንቅና ጠቃሚ መሆናቸው፤ መቼም ቢሆን እስከዘላለሙም አይሻርም። የኛ ማወቅና አለማወቅ፤ የኛ ማጨብጨብና አለማጨብጨብ አይደለም። ብናውቅና ብናጨበጭብ ጥሩ ነው። ግን፤ ባናውቅና ባናጨበጭብም እንኳ፤ የጀግኖቹ ተግባር ጠቃሚ ሆኑን ልንሽረው አንችልም። እውነት ነውና። ዘላለማዊ ነው። ይህንን የሚያውቁ ጀግኖች፤ በህይወት ዘመናቸው ውስጥ በእያንዳንዱ ድንቅ ብቃትና መልካም ተግባር ዘላለማዊ የህይወት ደስታን ያጣጥማሉ።
ጀግኖች፤ ስኬታቸውና ራዕያቸው፤ እውነተኛና ብሩህ መሆኑን ሲያውቁ፤ እውነተኛነቱና ብሩህነቱ በየትኛውም ጊዜ እንደማይሰረዝ እንደማይደለዝ ይገነዘቡታል፤ እናም በዚያው ልክ ዘላለማዊ ህልውናንን ያጣጥማሉ። ከሊዊ ፓስተር ፔኒሲሊን፤ ከአርኪሜደስ የፈሳሽ ነገሮች ህግ፤ ከአንስታይን የኢነርጂ ቀመር ጀምሮ፤ እያንዳንዷ የእውቀት ግኝት፤ የቴክኖሎጂ ፈጠራና የምርት ውጤት፤ በብሩህ ራዕይ የታጀበች እውነተኛ ስኬት መሆኗ... ለዘላለም እውነት ነው።  መሞት ይህንን አይሰርዘውም።
የህይወት ትርጉምም ይሄው ነው - እንዲህ መቼም ዘላለምም ሊሰረዝና ሊሻር በማይችል፤ ከአስተዋይነት በመነጨ ትክክለኛ ሃሳብ፤ በድንቅ ብቃትና በመልካም ተግባር፤ በድንቅ ስኬትና በብሩህ ራዕይ ህይወትን ማጣጣም ነው የህይወት ትርጉም። ጨለማውን መንፈስ አሽቀንጥረን መጣል የምንችለው፤ ከሞት በኋላና ከሞት ወዲያ ማዶ አሻግረን ለመቃኘት በመፍጨርጨር አይደለም። ዘላለማዊ ህልውናና የህይወት ትርጉም ያለው፤ እዚሁ በህይወት ዘመን በምናሳልፋቸው ደቂቃዎችና ሰዓታት፤ ቀናትና አመታት ውስጥ ነው።
ህይወትና ሞት የግል ነው። መጋራት አይቻልም። ሁሉም ሰው በየግሉ ይሞታል፤ በዚህ በዚህ ሁላችንም እንመሳሰላለን። ነገር ግን፤ ሁሉም ሰው ህይወትን አያጣጥምም። የምናደንቃቸው ጀግና ሰዎች፤ ዘላለማዊ የህይወት ደስታን አጣጥመዋል። አድናቆታችን ትርጉም የሚኖረው፤ እኛም እንደየአቅማችን ያንን የህይወት ጣእም ለማጣጣም ስንነቃቃ ነው።
*****************************************************************************
 ምንጭ:--http://www.addisadmassnews.com

ረቡዕ, ኖቬምበር 21, 2012

“የፊደል ገበታ አባት”

የ”ሀለሐመ” ፊደል ገበታ ፈጣሪ ማነው?
ተስፋ ገብረስላሴ
**********
ከዛጉዬ ስርወ መንግስት በኋላ ግዕዝን ተክቶ ለንግግርና ለፅሁፍ ማገልገል የጀመረውና “የመንግስት የስራ ቋንቋ” የሆነው አማርኛ፤ ግዕዙን የፊደል ገበታ የቀረፀው ማንና መቼ እንደሆነ ለማወቅ ጉጉት እንደፈጠረው ሁሉ የአማርኛው “ሀለሐመ” የሚለውም እንዴት፣ መቼና በእነማን ተፈጠረ ብሎ መጠየቅ አጓጊ ነው፡፡“የፊደል ገበታ አባት” የሚል ቅፅል መጠሪያ ያገኙት ተስፋ ገብረስላሴን የህይወትና የስራ ታሪክ የሚያስቃኘው መፅሃፍ፤ ስለአማርኛ የፊደል ገበታ ፈጣሪዎች ማንነትና ዘመን ማብራሪያ ባይኖረውም፣ ባለታሪኩ በመጀመሪያ በብራና ላይ በእጃቸው እየፃፉ፣ በመቀጠልም በማተሚያ ቤት ማሽን እያባዙ ለህዝብ እንዲደርስ ያደረጉት “የአማርኛ የፊደል ቅርፅ በወቅቱ በእንጦጦ ማርያም፣ በባዓታ ለማርያምና በመካነየሱስ ስላሴ አጥቢያዎች እንዲሁም በገጠር አብያተ ክርስትያናትና በገዳማትና በዋሻዎች ብቻ ተወስኖ” እንደነበር መረጃ ይሰጣል፡፡
ይህ ፍንጭ አጥኚዎች የፊደል ገበታውን በእነዚህ ተቋማት ያኖረውስ ማነው ብለው እንዲጠይቁ የሚያግዝ ጥቆማ ነው፡፡
ለ100 ዓመት ሴተኛ አዳሪዎች ያልተለዩት መንደር
ተስፋ ገብረስላሴ በ1909 ዓ.ም የ15 ዓመት ልጅ ሆነው ከትውልድ መንደራቸው ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ ያረፉበት መንደር አራት ኪሎ ነበር፡፡
በዚያ ዘመን ከአራት ኪሎ መንደሮች አንዱ በሆነው “እሪ በከንቱ ደንበኛ መጠጥ ቤቶችና ጥሩ ጥሩ ሴተኛ አዳሪዎች የሚገኙበት የከተማይቱ ደማቅ አካባቢ ፤አዝማሪና ሸላይ የማይታጣበት የቆንጆዎች መቀጣጠሪያ ነበር” ይላል በመፅሃፉ ገፅ 29 የሰፈረ መረጃ፡፡ የፓርላማ ማስፋፊያና የባሻ ወልዴ ችሎት መንደር ለዳግም ልማት ባይፈርስ ኖሮ ሴተኛ አዳሪነት ሁለተኛውን ምዕተ ዓመት ማስቆጠሩ አይቀርም ነበር ወይ ያሰኛል - መረጃው፡፡
ይፍረስ የተባለው የነጋድራስ አቡነከር ቤት
ተስፋ ገብረስላሴ አዲስ አበባ ከመጡ በኋላ ሰርተው ራሳቸውን ለመቻል በእንጨት ፈለጣ፣ ውሃ በመቅዳት፣ ጉድጓድ በመቆፈር፣ በጎዳና ንግድ እና መሰል ትናንሽ ስራዎች ላይ ተሳትፈዋል፡፡ ነጋድራስ አቡበከር ከጅቡቲ ከሚያስመጧቸው በተለይ ሽቶ እየተቀበሉ በየሆቴሉ ዞረው ሸጠዋል፡፡በዘመኑ በአራት ኪሎ መንደር በንግድ ስራቸው በጣም ታዋቂ የነበሩት ነጋድራስ አቡበከር የአፋር ብሄረሰብ ተወላጅ ነበሩ፡፡
ከፈረንሳይ አገር የሚያስመጡትን ሸቀጥ በጅቡቲ በኩል ወደ አዲስ አበባ በማስገባት አገልግሎት ሲሰጡ በዕድሉ ከተጠቀሙት አንዱ የነበሩት ተስፋ ገብረስላሴ፣ በኋለኛው ዘመን ላይ የነጋድራስ ግቢ ለሽያጭ ሲቀርብ ገዝተው ባለንብረት መሆኑ ቻሉ፡፡ ከህትመት ስራ ጋር የተያያዘ ከ100 ዓመት በላይ ታሪክ ያለው ግቢ ከባሻ ወልዴ ዳግም ልማት ስም ይፍረስ መባሉና ከዚህ ጋር የታዩ ክስተቶች ምን እንደሚመስሉ “ዘመን ተሻጋሪ ባለ-ውለታ” ታሪክን አስፍሮ መማሪያ እንዲሆን ማድረግ ችሏል፡፡
መንግስት በከተሞች ያገኘው ቤንዚን
በአሁኑ ወቅት በአገራችን ኢትዮጵያ እየተመዘገበ ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት የነዳጅ ምርትን መሰረት ያደረገ አለመሆኑ ብዙዎችን እንዳስደመመ ይታወቃል፡፡ ካሁን በፊት በመንግስትና በህዝብ የተሰሩትን ሳይጨምር በአምስት ዓመት የትራንስፎርሜሽን እቅድ ተግባራዊ እንዲሆኑ የታቀዱ ሃሳቦችን ለመንደፍ መንግስትን የልብ ልብ የሰጠው ምንድነው ለሚለው ጥያቄ አንዱ መልስ “መንግስት በከተሞች ያገኘው ቤንዚን ነው” የሚል ነው፡፡
ዛሬ በከተማ የሚገኝ አንድ ሜትር ካሬ የመሬት ዋጋ ስንት እየተከፈለበት ነው ለሚለው ጥያቄ አንባቢ ከያለበት ሆኖ የሚያውቀውንና የሰማውን ለራሱ መልስ በመስጠት ያግዘኛል፡፡ የዛሬ 70 ዓመት በአዲስ አበባ ከተማ ያውም በአራት ኪሎ መንደር ለአንድ ሜትር ካሬ መሬት የተከፈለው ከፍተኛው ገንዘብ 2 ብር ከ35 ሳንቲም ነበር፡፡ የተስፋ ገብረስላሴ ማተሚያ ቤት የሚገኝበት ግቢ ከመጀመሪያው ባለይዞታ ወደ ሁለተኛው ባለሃብት የዞረው በዚህ ሽያጭ እንደነበር የ“ዘመን ተሻጋሪ ባለ-ውለታ” መረጃ ለአንባቢያን አቀብሏል፡፡ ለካንስ መንግስት ለታሪክና ለቅርስ ደንታ የሌለው መስሎ የሚታየው ለ “ነዳጁ” የተለየ ክብርና ዋጋ ስለሰጠ ነውም ያስብላል - መረጃው፡፡
የሚስተር ዴቪድ ውለታ
በ1990ዎቹ አጋማሽ በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ በወጣ ዜና፤ “የመጀመሪያውን የአማርኛ መፅሃፍ ቅዱስ ተርጉሞ ለህዝብ የቀረበው በዓፄ ቴዎድሮስ ዘመነ መንግስት ከእንግሊዝ የመጣ ሚስዮናዊ ነው፡፡” የሚል ማንበቤን አስታውሳለሁ”” የተስፋ ገብረስላሴን የህይወትና የስራ ታሪክ በሚያስቃኘው መፅሃፍ ውስጥ በአፄ ቴዎድሮስ ዘመን ለወንጌል አገልግሎት ስለመጣ የካቶሊክ ሚሲዮናዊ ስለ ሚስተር ዴቪዲም ያነሳል፡፡
የኤደን ዜግነት የነበረው ሚስተር ዴቪድ፤ ከአፄ ቴዎድሮስ ህልፈት በኋላ በአፄ ምኒልክ ዘመን ወደ አዲስ አበባ በመምጣት “ፒያሳ በተባለው አካባቢ በአሁኑ ሲኒማ አምፒር መደዳ ካለ በአንደኛው ሰቀላ ቤት ላይ መፅሃፍ ቅዱስ እያሳተመ፣ አንዱን መፅሃፍ በአንድ ብር (ማርያትሬዛ) ማንበብና የመግዛት አቅም ላላቸው ሰዎች በየቤታቸው እያንኳኳ ይሸጥ እንደነበር ተገልጿል፡፡
የዚህ ሰው ተግባርና ውለታ ብቻውን በመፅሃፍ በቀረበለት የሚያሰኝ ነው፡፡ የክርስትና ሃይማኖት ለአገራችን የህትመት ዘርፍ፣ ለአማርኛ ቋንቋ ዕድገት፣ ለመፅሃፍ መሸጫ መደብሮች መከፈት፣መፅሃፍ አዙሮ የመሸጥ ስራ ለመጀመር… ቀላል የማይባል አስተዋጽኦ አበርክቷል፡፡
ክስ፣እስርና ውንጀላ ያልተለያቸው ባለታሪክ
የተስፋ ገብረስላሴን የስራና የህይወት ታሪክን ማዕከል አድርጎ የአገራችንን ማህበራዊ ፣ፖለቲካዊ፣ኢኮኖሚያዊና ባህላዊ ጉዳዮች በስፋት የሚያስ(ነኘው “ዘመን ተሻጋሪ ባለ-ውለታ” መፅሃፍ፤ ባለ ታሪኩ የህዝብና የአገር ባለውለታ መሆን የቻሉት በብዙ ውጣ ውረድ ውስጥ አልፈው እንደሆነ ይገልፃል፡፡
በንጉሱ ዘመን (ከኢጣሊያ ወረራ በፊትና በኋላ) ፣በጠላት ወረራ ወቅት፣ በደርግም አገዛዝ ለክስ፣ ለእስርና ውንጀላ ተዳርገዋል፡፡ በመጨረሻ ሁሉንም አሸንፈው በተደጋጋሚ ተሸላሚ ሆነዋል፡፡ ከአፄ ኃይለስላሴ መንግስት የቀኝአዝማች ማዕረግ ተሰጥቷቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር ደጋግሞ አመስግኗቸዋል፡፡
ሞትን መቅደም
ታላቅ ተግባርና ትልቅ ስም አርቆ መድረሻን ለማቀድ፣ከብዙ ጥረትና ልፋት የሚገኝ ነው፡፡ በአመታት ድካም የተገነባ መልካም ተግባርና ስም ሊጠፋ፣ ሊረሳና ሊዘነጋ የሚችልባቸው ብዙ ምክንያቶች አሉ፡፡ እኔ ከሞትኩ በኋላ ጥረትና ድካሜ ምን ይሆናል ብሎ ቀድሞ አለማሰብ ታላቅ ተግባርና ስም እንዲጠፋ ሰበብ ከሚሆኑት አንዱ ነው፡፡ ቤተሰቦቻቸውን ባለ አክሲዮን በማድረግ ኃ.የተ.የግ.አ/ማህበር በ1991ዓ.ም ያቋቋሙት ባለታሪኩ፤ ስራና መልካም ተግባራቸው እንዳይጠፋ ማድረግ ችለዋል፡፡
ለሟች መታሰቢያ ሐውልት ይሻላል ቤተ መፅሃፍት
ተስፋ ገብረስላሴ ግንቦት 26 ቀን 1992ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ፣ የ97 ዓመት የዕድሜ ባለፀጋ ነበሩ፡፡ ከመሞታቸው በፊት የቀብር ቦታቸውን በስላሴ ካቴድራል ለማዘጋጀት አስበው የነበረ ቢሆንም የአርበኞች ማህበር አርበኝነታቸውን አላውቅም ስላለ ቀብራቸው በእንጦጦ ኤልያስ ቤተክርስቲያን ተፈፅሟል፡፡ ባለ ሁለት ክፍል መቃብር ቤት ቤተ መፅሃፍት ሆኖ እንዲያገለግል ስለታሰበም በውስጡ ከ300 በላይ መፅሀፍት ይዟል፡፡
ይህ በአገራችን በስፋት ሊለመድ የሚገባ ጥሩ ጅማሮ ነው፡፡ “የፊደል ገበታ አባት” የሚል ቅዱስ መጠሪያ ያላቸው የቀኝ አዝማች ተስፋ ገብረስላሴን የህትመትና የስራ ታሪክ የሚያስቃኘውን መፅሃፍ የማስተዋወቅ ዳሰሳዬን የማጠቃልለው የዚህ ዓይነት መፅሃፍት ህትመት ቁጥር እየተበራከተ መምጣቱ ይበል የሚያሰኝ መሆኑን ገልጬ ነው፡፡
************************************************
ምንጭ:==http://www.addisadmassnews.com

ሰኞ, ኖቬምበር 12, 2012

ጋዜጠኛ ደምሴ ዳምጤ

"ዳኙ ገላግለን"

 1945-2005

‹‹ዳኙ ሊመታ ነው፤ ዳኙ ገላግለን . . . ወይኔ ዳኙ አ - ገ - ባ -፤ ደንሶ አገባ ዳኙ፣ ቀኝ አሳይቶ ግራ፣ ግራ አሳይቶ ቀኝ በጣም አስደናቂ ግብ ነው . . . ›› ትንፋሹ ቁርጥ ቁርጥ እያለ ደስታና ሲቃ፣ ስሜትም በተቀላቀለበት ድምፀት ታኅሣሥ 17 ቀን 1980 ዓ.ም. ያስተጋባው ታዋቂው የስፖርት ጋዜጠኛ ደምሴ ዳምጤ ነበረ፡፡
ኢትዮጵያ ያዘጋጀችውን 15ኛው የምሥራቅና መካከለኛው አፍሪካ ዋንጫ ከ25 ዓመት በፊት ያገኘችበትን ድል በራዲዮ ሞገድ አሳብሮ ድምፁን፣ እስትንፋሱን ያሰማው ጋዜጠኛ ደምሴ ትናንት ነበር፣ ዛሬ ግን የለም፣ ከአፀደ ሥጋ ተለየ፤ አረፈ፡፡

በኢትዮጵያ ስፖርት ጋዜጠኝነት ታሪክ ሁነኛ ሥፍራ ያለው ደምሴ፣ የስፖርት ዜናዊነቱን የጀመረው ምሥራቃዊቷ ድሬዳዋ ከተማ በአማተርነት እየዘገበ ወደ አዲስ አበባ መላክ በጀመረበት ጊዜ ነው፡፡ በተለይ በኢትዮጵያና ብሥራተ ወንጌል ሬዲዮ ጣቢያዎች፣ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥንም ጋዜጠኛና ‹‹የስፖርት ፋና›› ጋዜጣ መሥራች ከነበረው ታላቁ ጋዜጠኛ ሰሎሞን ተሰማ ጋር ቅርበት ስለነበረው ከድሬዳዋ የሐረርጌን ስፖርታዊ እንቅስቃሴ እየዘገበ ይልክ ነበር፡፡

ኢትዮጵያ 10ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ካስተናገደችባቸው ከተሞች አንዷ ደምሴ ዳምጤ የነበረባት የኖረባት ድሬዳዋ የእግር ኳስ ዘገባ ትሩፋት ያቀረበባትም ነች፡፡ ለአገሪቱ ስፖርት ዕድገት በተለይም እግር ኳሱ እንዲያብብ በሙያው ያደረገው ጥረት ኢትዮጵያውያን ተጫዋቾች ክሂላቸው ከማንም እንደማያንስ በማንፀባረቅ ነበር፡፡ በ1970ዎቹ መጨረሻና በ80ዎቹ መጀመርያ ጎልተው ወጥተው የነበሩት እነሙሉጌታ ከበደ፣ ሙሉጌታ ወልደየስ፣ ገብረመድኅን ኃይሌን ሲያወድስ ገጣሚ ሆኖ በመገኘት ነበር፡፡

‹‹የምን ማራዶና የምን ፔሌ ፔሌ
እኛም አገር አለ ገብረመድኅን ኃይሌ›› ጎልታ የምትጠቀስለት መንቶ ግጥሙ ነበረች፡፡

በዘመኑ እየበረከቱ የመጡት ወጣት ጋዜጠኞች አርአያቸው እንደሆነ የሚናገሩለት ደምሴ፣ ሦስት ኦሊምፒኮች የዓለም ሻምፒዮናዎች፣ የአገር አቋራጭ ውድድሮችን እየተመለከተ ዜናውን አድርሷል፡፡

ጋዜጠኛ ደምሴ ተወልዶ ያደገው ድሬደዋ ሲሆን ከ33 ዓመት በፊት በኢትዮጵያ ሬድዮ ከመቀጠሩ በፊት የስፖርት ፊሪላንስ ጋዜጠኛ ሆኖ ከትውልድ ስፍራው ይሰራ ነበር፡፡

ጋዜጠኛ ደምሴ ለኢትዮጵያ ስፖርት እድገት ደከመኝ ሳይል የሰራና በዚህም በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈ ባለሙያ ነበር፡፡

በሙያውም አትላንታ፣አቴንስና ቤጅንግ ኦሎምፒኮችን በስፍራው በመገኘት ለኢትዮጵያ ህዝብ አስተላልፏል፡፡


ከአባቱ አቶ ደምሴ ሳልለውና ከእናቱ ወይዘሮ ታየነው በሐረርጌ ጠቅላይ ግዛት ጋራ ሙለታ የተወለደው ጋዜጠኛ ደምሴ፣ ባደረበት ሕመም ምክንያት ሕክምናውን በአገር ውስጥና በውጭ ሲከታተል ቆይቶ ጥቅምት 26 ቀን 2005 ዓ.ም. አርፏል፡፡ ሥርዓተ ቀብሩም ትናንትና በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አባዱላ ገመዳ፣ የመንግሥት ሹማምንትና የስፖርት ቤተሰቦች በተገኙበት ተፈጽሟል፡፡ ጋዜጠኛ ደምሴ ዳምጤ ባለትዳርና የሦስት ልጆች አባት ነበረ፡፡

ደምሴ ኢትዮጵያ በ1980 ለምሥራቅና መካከለኛው አፍሪካ አገሮች ሻምፒዮና(ሴካፋ) ከዚምባብዌ ጋር አዲስ አበባ ላይ ለፍጻሜ በፍጹም ቅጣት በደረሰችበት ወቅት ዳኛቸው ደምሴ በመጨረሻ ለሚመታት ምት ''ዳኙ ገላግለን''ብሎ በሬዲዮ ባስተላለፈው የቀጥታ ስርጭት ሳቢያ ብዙዎች ይህንኑ እንደ ቅጽል ስም አድርገውለት መቅረቱም ይታወቃል።

ከአንጋፋዎቹ ዝነኛና ታዋቂ የአገራችን የስፖርትጋዜጠኞች ሰለሞን ተሰማ ነጋ ወልደስላሴና ፍቅሩ ኪዳኔ ቀጥሎ በ1962 ዓ.ም. ከድሬ ደዋ በአማተር የስፖርት ዜና ዘጋቢነት ለ ሰባት አመታት በመቀጠልም በኢትዮጵያ ሬድዮ ድርጅት እስካሁን ለ33 ዓመታት ባጠቃላይ ከ40 ዓመት በላይ የስፖርት ጋዜጠኛ በመሆን ያገለገለ ታዋቂና ዝነኛው ጋዜጠኞ ደምሴ ዳምጤ -
- በሞስኮ ፤ በሎሳጀለስ ፤ በሴኦል ፤ በባርሴሎና ፤ በአትላንታ ፤ በሲድኒ ፤ በአቴንስና በቤጂንግ የኦሎምፕክ ጨዋታዎች ባቀረባቸው የስፖርት ዘገባዎች፤
- በዓለምና የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የእግር ኳስ ጨዋታዎች ባስተላለፈው የእግር ኳስ ቀጥታ ስርጭት፤
- በዓለም አትሌትክስ ሻምፒዮንና በመላ አፍሪካ ጨዋታዎች፤
*******************************************************************************
 ምንጭ:--http://www.ethiopianreporter.com
             http://ethiopianobserver.wordpress.com/
             http://shegertribune.blogspot.com
            

ማሞ ካቻ (አቶ ማሞ ይንበርብሩ)

  አቶ ማሞ ይንበርብሩ (ማሞ ካቻ) እስቲ እናስታውሳቸው፣ ተቀብሮ እንዳይቀር አኩሪ ታሪካቸው  (ደረጀ መላኩ)   አቶቢሲ ማሞ ካቻ የት ትሄዳለህ? ገብረ ጉራቻ… ታዳጊው ማሞ ይንበርበሩ ገና በጨቅላ እድሜው አባቱ አቶ...