ሰኞ, ኖቬምበር 12, 2012

ጋዜጠኛ ደምሴ ዳምጤ

"ዳኙ ገላግለን"

 1945-2005

‹‹ዳኙ ሊመታ ነው፤ ዳኙ ገላግለን . . . ወይኔ ዳኙ አ - ገ - ባ -፤ ደንሶ አገባ ዳኙ፣ ቀኝ አሳይቶ ግራ፣ ግራ አሳይቶ ቀኝ በጣም አስደናቂ ግብ ነው . . . ›› ትንፋሹ ቁርጥ ቁርጥ እያለ ደስታና ሲቃ፣ ስሜትም በተቀላቀለበት ድምፀት ታኅሣሥ 17 ቀን 1980 ዓ.ም. ያስተጋባው ታዋቂው የስፖርት ጋዜጠኛ ደምሴ ዳምጤ ነበረ፡፡
ኢትዮጵያ ያዘጋጀችውን 15ኛው የምሥራቅና መካከለኛው አፍሪካ ዋንጫ ከ25 ዓመት በፊት ያገኘችበትን ድል በራዲዮ ሞገድ አሳብሮ ድምፁን፣ እስትንፋሱን ያሰማው ጋዜጠኛ ደምሴ ትናንት ነበር፣ ዛሬ ግን የለም፣ ከአፀደ ሥጋ ተለየ፤ አረፈ፡፡

በኢትዮጵያ ስፖርት ጋዜጠኝነት ታሪክ ሁነኛ ሥፍራ ያለው ደምሴ፣ የስፖርት ዜናዊነቱን የጀመረው ምሥራቃዊቷ ድሬዳዋ ከተማ በአማተርነት እየዘገበ ወደ አዲስ አበባ መላክ በጀመረበት ጊዜ ነው፡፡ በተለይ በኢትዮጵያና ብሥራተ ወንጌል ሬዲዮ ጣቢያዎች፣ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥንም ጋዜጠኛና ‹‹የስፖርት ፋና›› ጋዜጣ መሥራች ከነበረው ታላቁ ጋዜጠኛ ሰሎሞን ተሰማ ጋር ቅርበት ስለነበረው ከድሬዳዋ የሐረርጌን ስፖርታዊ እንቅስቃሴ እየዘገበ ይልክ ነበር፡፡

ኢትዮጵያ 10ኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ካስተናገደችባቸው ከተሞች አንዷ ደምሴ ዳምጤ የነበረባት የኖረባት ድሬዳዋ የእግር ኳስ ዘገባ ትሩፋት ያቀረበባትም ነች፡፡ ለአገሪቱ ስፖርት ዕድገት በተለይም እግር ኳሱ እንዲያብብ በሙያው ያደረገው ጥረት ኢትዮጵያውያን ተጫዋቾች ክሂላቸው ከማንም እንደማያንስ በማንፀባረቅ ነበር፡፡ በ1970ዎቹ መጨረሻና በ80ዎቹ መጀመርያ ጎልተው ወጥተው የነበሩት እነሙሉጌታ ከበደ፣ ሙሉጌታ ወልደየስ፣ ገብረመድኅን ኃይሌን ሲያወድስ ገጣሚ ሆኖ በመገኘት ነበር፡፡

‹‹የምን ማራዶና የምን ፔሌ ፔሌ
እኛም አገር አለ ገብረመድኅን ኃይሌ›› ጎልታ የምትጠቀስለት መንቶ ግጥሙ ነበረች፡፡

በዘመኑ እየበረከቱ የመጡት ወጣት ጋዜጠኞች አርአያቸው እንደሆነ የሚናገሩለት ደምሴ፣ ሦስት ኦሊምፒኮች የዓለም ሻምፒዮናዎች፣ የአገር አቋራጭ ውድድሮችን እየተመለከተ ዜናውን አድርሷል፡፡

ጋዜጠኛ ደምሴ ተወልዶ ያደገው ድሬደዋ ሲሆን ከ33 ዓመት በፊት በኢትዮጵያ ሬድዮ ከመቀጠሩ በፊት የስፖርት ፊሪላንስ ጋዜጠኛ ሆኖ ከትውልድ ስፍራው ይሰራ ነበር፡፡

ጋዜጠኛ ደምሴ ለኢትዮጵያ ስፖርት እድገት ደከመኝ ሳይል የሰራና በዚህም በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ያተረፈ ባለሙያ ነበር፡፡

በሙያውም አትላንታ፣አቴንስና ቤጅንግ ኦሎምፒኮችን በስፍራው በመገኘት ለኢትዮጵያ ህዝብ አስተላልፏል፡፡


ከአባቱ አቶ ደምሴ ሳልለውና ከእናቱ ወይዘሮ ታየነው በሐረርጌ ጠቅላይ ግዛት ጋራ ሙለታ የተወለደው ጋዜጠኛ ደምሴ፣ ባደረበት ሕመም ምክንያት ሕክምናውን በአገር ውስጥና በውጭ ሲከታተል ቆይቶ ጥቅምት 26 ቀን 2005 ዓ.ም. አርፏል፡፡ ሥርዓተ ቀብሩም ትናንትና በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አባዱላ ገመዳ፣ የመንግሥት ሹማምንትና የስፖርት ቤተሰቦች በተገኙበት ተፈጽሟል፡፡ ጋዜጠኛ ደምሴ ዳምጤ ባለትዳርና የሦስት ልጆች አባት ነበረ፡፡

ደምሴ ኢትዮጵያ በ1980 ለምሥራቅና መካከለኛው አፍሪካ አገሮች ሻምፒዮና(ሴካፋ) ከዚምባብዌ ጋር አዲስ አበባ ላይ ለፍጻሜ በፍጹም ቅጣት በደረሰችበት ወቅት ዳኛቸው ደምሴ በመጨረሻ ለሚመታት ምት ''ዳኙ ገላግለን''ብሎ በሬዲዮ ባስተላለፈው የቀጥታ ስርጭት ሳቢያ ብዙዎች ይህንኑ እንደ ቅጽል ስም አድርገውለት መቅረቱም ይታወቃል።

ከአንጋፋዎቹ ዝነኛና ታዋቂ የአገራችን የስፖርትጋዜጠኞች ሰለሞን ተሰማ ነጋ ወልደስላሴና ፍቅሩ ኪዳኔ ቀጥሎ በ1962 ዓ.ም. ከድሬ ደዋ በአማተር የስፖርት ዜና ዘጋቢነት ለ ሰባት አመታት በመቀጠልም በኢትዮጵያ ሬድዮ ድርጅት እስካሁን ለ33 ዓመታት ባጠቃላይ ከ40 ዓመት በላይ የስፖርት ጋዜጠኛ በመሆን ያገለገለ ታዋቂና ዝነኛው ጋዜጠኞ ደምሴ ዳምጤ -
- በሞስኮ ፤ በሎሳጀለስ ፤ በሴኦል ፤ በባርሴሎና ፤ በአትላንታ ፤ በሲድኒ ፤ በአቴንስና በቤጂንግ የኦሎምፕክ ጨዋታዎች ባቀረባቸው የስፖርት ዘገባዎች፤
- በዓለምና የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የእግር ኳስ ጨዋታዎች ባስተላለፈው የእግር ኳስ ቀጥታ ስርጭት፤
- በዓለም አትሌትክስ ሻምፒዮንና በመላ አፍሪካ ጨዋታዎች፤
*******************************************************************************
 ምንጭ:--http://www.ethiopianreporter.com
             http://ethiopianobserver.wordpress.com/
             http://shegertribune.blogspot.com
            

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ማሞ ካቻ (አቶ ማሞ ይንበርብሩ)

  አቶ ማሞ ይንበርብሩ (ማሞ ካቻ) እስቲ እናስታውሳቸው፣ ተቀብሮ እንዳይቀር አኩሪ ታሪካቸው  (ደረጀ መላኩ)   አቶቢሲ ማሞ ካቻ የት ትሄዳለህ? ገብረ ጉራቻ… ታዳጊው ማሞ ይንበርበሩ ገና በጨቅላ እድሜው አባቱ አቶ...