ልጥፎች

ጌታቸው ጋዲሳ__ኢትዮጵያ

ምስል
  የናፍቆት ትዝታሽ ካለን በሕይወት፣ ፍፁም የማንረሳሽ ውድ አገር እናት፤ ይኽ ነው አይባልም ክብር ኩራታችን፣ በነፃነት ስንኖር በኢትዮጵያዊነታችን ። 🎵🎵 🎵 ያብሮ አደግ ያብሮ አደግ ጓደኛ... ጓደኛ ትዝታው አይለቀን፣ ሜዳው ሸንተረሩ ሁሌ 'ሚናፍቀን፤ ናፍቆቱ ያደግንበት መንደር ... መንደር መቼ ይረሳና፣ ሌት ተቀን ብንባዝን ማን እንዳንቺ አለና፣ ክፉ አይንካሽ ሁኚ ደህና ክፉ አይንካሽ ሁኚ ደህና። 🎵🎵 🎵 የምሽት የንጋት ነፋሻ አየር፣ ከልብ የሚወደድ የሚፈቀር፤ በአእዋፋት ዝማሬ ታጅቦ፣ ሌሊቱ ነጋ ... ነጋ በፍቅር ታጅቦ፣ ተውቦ። ወግና በዓሉ ያገራችን፣ ያ ውዳመት የሰንበት ኅብረታችን፤ የክረምት የበጋ፣ ባለፀጋ፣ ኢ ት ዮ ጵ ያ ... ኢ ት ዮ ጵ ያ ለምለሚቷ ሸጋ ... ሸጋ። 🎵🎵🎵 ውዲቷ እናት ዓለም ለኛ ... ለኛ ምትክ የሌለሽ፣ ከአይምሮ አይጠፋም ያንቺ ትዝታሽ፤ በፍቅር አየርና ምድርሽ ... ምድርሽ ለሁሉ 'ሚስማማ፣ የደግ ምሳሌ ውብ ዓለም እማማ፤ ምድርሽ ደጉ የሚለማ የደግ ምሳሌ ውብ ዓለም እማማ፤ ምድርሽ ደጉ የሚለማ። 🎵🎵 🎵 ብዙ ውለታን አለሽ በልጆችሽ፣ መኖር እንመርጣለን ሳንለይሽ፤ ፍቅርሽ በልባችን የሚኖር፣ ማንም አይለየን ካንቺ ከሞት በቀር ... በቀር። የአያት የቅድመ አያት ታላቅ ቅርስ፣ ጎራዴ ጋሻቸው ሲታወስ፤ በቅኝ ያልተገዛሽ መሬታችን፣ ነፃነት ነው ክብራችን፣ የጀግንነታችን። ወግና በዓሉ ያገራችን፣ ያውዳመት የሰንበት ኅብረታችን፤ የክረምት የበጋ፣ ባለፀጋ፣ ኢ ት ዮ ጵ ያ ... ኢ ት ዮ ጵ ያ ለምለሚቷ ሸጋ ኢ ት ዮ ጵ ያ ... ኢ ...

«የሬዲዮ ቀን»ን የማያከብሩት ሬዲዮ ጣቢያዎች

ምስል
በ አንተነህ ቸሬ በየዓመቱ የካቲት 13 (እ.አ.አ) የዓለም የሬዲዮ ቀን (World Radio Day) ተከብሮ ይውላል ።የዓለም የሬዲዮ ቀን ሬዲዮ ለዓለም ያበረከተውንና እያበረከተ ያለውን አስተዋጽኦ የማሰብና የሬዲዮን ልዩ ገፅታዎች/ባህርያት የማስገንዘብ ዓላማ አለው ። በዕለቱ ሬዲዮ ከሌሎቹ የመገናኛ ብዙኃን ዘርፎች ስለሚለይባቸውና ተመራጭ ስለሚሆንባቸው ባህርያቱ እንዲሁም ሬዲዮ ለዓለም ሕዝብ ስላበረከታቸው አስተዋፅኦዎችና ስለዋላቸው ውለታዎች በስፋት የሚነገርበትና የሚዘመርበት ነው ።ሬዲዮ ያሉበትን ውስንነቶች ስለማሻሻልና ስላጋጠሙት ችግሮችም ይመከራል ። እ.አ.አ በ2010 የስፔን የሬዲዮ አካዳሚ (Span­ish Radio Academy) ዓለም አቀፍ የሬዲዮ ቀን (World Radio Day) እንዲሰየም ለአገሪቱ መንግሥት ጥያቄ አቀረበ ።የስፔን መንግሥትም የአካዳሚውን ጥያቄ ተቀብሎ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ተቋም (UNESCO) አቀረበ ። የተቋሙ ሥራ አስፈፃሚ ቦርድ ለተቋሙ ጠቅላላ ጉባዔ ባቀረበው ምክረ ሃሳብ መሠረት የካቲት 13 (እ.አ.አ) የዓለም የራዲዮ ቀን ሆኖ በየዓመቱ እንዲከበር እ.አ.አ በ2011 ውሳኔ አስተላለፈ ።ቀኑ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሬዲዮ (UN Radio) ከተቋቋመበት ቀን (እ.አ.አ የካቲት 13 ቀን 1946 ዓ.ም) ጋር ይገጣጠማል ። የመጀመሪያው የዓለም የሬዲዮ ቀን የተከበረው እ.አ.አ በ2012 ሲሆን በወቅቱ በእንግሊዝ፣ በስፔን፣ በስዊዘርላንድ፣ በኢጣሊያ፣ በባንግላዴሽና በሌሎች አገራት በልዩ ልዩ መሰናዶዎች ተከብሮ ነበር ።በጊዜው አንዳንድ አገራት የቀኑን አከባበር የሚከታተሉና የሚቆጣጠሩ ልዩ ኮሚቴዎችንም አቋቁመው ነበር ። የተለያዩ አገራት ቀኑን በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ያከብሩታል ።በሬዲዮ ጣቢያዎች ከ...

መስከረም የወራቱ ጌታ

ምስል
ሔኖክ ያሬድ << መስከረም አበባ መስከረም አበባ ፣       እንቁጣጣሽ መጣ አዲስ ዓመት ገባ ፤       መስከረም ሲጠባ አደይ ሲፈነዳ፣       እንኳን ሰው ዘመዱን ይጠይቃል ባዳ ። >> የኢትዮጵያ የወራት ሁሉ መጀመሪያ መስከረም ነው፡፡ ‹‹ ኢዮሃ አበባዬ . . . መስከረም ጠባዬ ›› ዘመን በተሞሸረ ዓመት በተቀመረ ቁጥር ሰው መልካም ምኞት የሚለዋወጥበት ሐረግ ነው፡፡ ድምፃውያንም ያቀነቅኑታል፡፡ እንግዲህ ኃያሉ ክረምት ሊያበቃ፣ መሰስ እያለ ወጥቶ ለከርሞ ሊመለስ ከመስቀል በዓል በኋላ ሁለት ሳምንት ( መስከረም 25 ቀን 2012 ዓ . ም .) ቢቀረው ነው፡፡ በመጻሕፍት እንደተጠቀሰው፣ ኢዮሃ አበባዬ የደስታ ቃል ነው፡፡ ወንዶች የደመራ ለት እየዘፈኑ ድምሩን የሚዞሩበት ያበባ ዘፈን ነው፡፡ ሰኔ ግም ብሎ፣ ያምሌን ጨለማ አልፎ፣ የነሐሴን ጎርፍ ሙላትን በእኝኝ ተሻግሮና ተንተርሶ በጠንካራው ዝናብ ( ውሃ ) ምክንያት ብቅ የምትለዋ ያደይ አበባ ናትና፤ ውሃ ያደረገውን ታምር፣ ያስበቀለውን አበባ አደያዊን ተመልከት ለማለት ‹‹ ኢዮሃ አበባዬ መስከረም ጠባዬ ›› ይባላል፡፡ ታዋቂው ደራሲ በዓሉ ግርማ ‹‹ ደራሲው ›› በተሰኘው ልቦለዱ የመስከረምን ድባብ የገለፀበት አገላለጹ አዲሱ ዓመት በመጣ ቁጥር ሁሌ የሚታወስ ነው፡፡ ‹‹ መስከረም ጠባ፡፡ የመስከረም ጮራ ዕንቁጣጣሽ ብላ ተግ አለች፡፡ ልጃገረዶች ሳዱላቸውን አሳመ...