ልጥፎች

ሲልቪያ ፓንክረስት - የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ወዳጅ

በፍቅር ለይኩን እንግሊዛዊቷ ሚስስ ሲልቪያ ፓንክረስት በ1953 ዓ.ም. በወርሀ መስከረም በመስቀል በዓል ዕለት  አርፈው የቀብራቸው ሥነ ስርዓት በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የተፈጸመው በማግስቱ መስከረም 18 ቀን ነበር፡፡ ሲልቪያ ፓንክረስት የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ወዳጅ፣ የሰብአዊ መብት ታጋይ፣ ኢትዮጵያ በኢጣሊያን በተወረረችበት ጊዜም ወረራውን በመቃወም የፀረ ፋሽስት ዘመቻን በአውሮፓ ያስፋፉ፣ የፋሽስትን ኢሰብአዊ የሆነ ጭፍጨፋና ግፍ ያጋለጡ፣ የሰው ልጆች መብትና ነፃነት ተቆርቋሪ የሆኑ በታሪክ ትልቅ ስፍራ የተሰጣቸው ታላቅ ሴት ናቸው፡፡ ሲሊቪያ ፓንክረስት ታጋይ ብቻ ሳይሆኑ የታሪክ ተመራማሪና ጸሐፊም ናቸው፡፡ እኚህን የኢትዮጵያን የቁርጥ ቀን ወዳጅ የሞቱበትን 52ኛ ዓመት በማስመልከት ታሪካቸውን በጥቂቱ ልንዘክረው ወደድን፡፡ ሲልቪያ ፓንክረስት የተወለዱት ሚያዝያ 27 ቀን 1874 ዓ.ም. በእንግሊዝ አገር ማንችስተር በተባለው ከተማ ነው፡፡ ለሲልቪያ ፓንክረስት የወደፊት ሕይወት ላይ ደማቅ አሻራን ያኖሩት አባታቸው ዶ/ር ሪቻርድ የእንግሊዝ ሌበር ፓርቲ ንቁ ተሳታፊ፣ ለድሆች ተሟጋችና መብታቸውን ለተነፈጉ ሁሉ ድምፅ ነበሩ፡፡ እናታቸው ኤምሊ ፓንክረስትም ሴቶች  በእንግሊዝና በአውሮፓ ፖለቲካና ምርጫ ውስጥ ንቁ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ትልቅ ሚና የተጫወቱና ብርቱ ትግል ያደረጉ ሴት ነበሩ፡፡ ሲልቪያ የአባታቸውንና እናታቸውን አርአያ በመከተል ዕድሜ ዘመናቸውን ሁሉ ለሰው ልጆች መብትና ነፃነት በመታገል አሳልፈዋል፡፡ በ1928 ዓ.ም. ወራሪው ፋሽስት ኢጣሊያ የኢትዮጵያን ሕዝብ በመርዝ ቦምብ ሲፈጅና የፍትሕ ያለህ እያለ በሚጮኽበት፣ ኢትዮጵያውን አርበኞች በዱር በገደል ለአገራቸው ነፃነት ደማቸውን በማፍሰስ ላይ በነበሩበት ጊዜ ...

የአማርኛ ፊደል ክርክር በታይፕራይተር ዘመን

የአማርኛ ፊደል ክርክር በታይፕራይተር ዘመን  ዮናስ ብርሃኔ   በንጉሡ ዘመን ነው፡፡ ታይፕራይተር ወደ አገራችን እንደገባ ሰሞን በአጠቃቀም ዙሪያ ውዝግብ ተነስቶ የነበረ ሲሆን እነ መንግሥቱ ለማም ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አደባባይ መድረክ ብቅ ያሉበት አጋጣሚም ነበር፡፡ መንግሥቱ ለማን ጨምሮ ሌሎች ወጣት ተማሪዎች የትምህርት እድል አግኝተው ወደ እንግሊዝ ለመሄድ እየተዘጋጁ በነበረበት ወቅት፣ በአራት ኪሎ ቅድስት ሥላሴ ግቢ ደግሞ በአማርኛ ፊደል ዙሪያ ቅልጥ ያለ ክርክር እየተካሄደ ነበርና ወጣቶቹ ተማሪዎቹም እዚያ ላይ እንዲገኙ በትምህርት ሚኒስቴር ተጋብዘው ይሄዳሉ፡፡ ነገሩን ራሳቸው መንግሥቱ ለማ እንደገለፁት በማለት ንቡረ እጽ ኤርምያስ ከበደ ስለ ሁኔታው ሲያትቱ፤ ..መንግሥቱ ከሌሎች ወዳጆቹ ጋር ወደ ጉባኤው ሲገቡ ሁለቱ ቀንደኛ ተከራካሪዎች የወቅቱ ጤና ጥበቃ ሚኒስትር አቶ አበበ ረታ እና በቤተመንግሥት የታሪክና የመጻሕፍት ሹም የነበሩት ብላታ መርሰዔ ሀዘን ወልደ ቂርቆስ የጉባኤው ሊቀመንበር እና በጊዜው የሥራ ሚኒስትር ከነበሩት ብላታ ዘውዴ በላይነህ ግራ እና ቀኝ ተቀምጠው ነበር፡፡ እነሱ በገቡበት ሰዓት የነበረው ድባብ ..በላቲኑ ሥርዓት፣ በላቲኑ ፊደል እንጻፍ.. የሚለው የብላታ መርስዔ ኅዘን ሃሳብ ወደመሸነፉ አጋድሎ፣ ቅጥሉን አንድ አይነት አድርገን አሻሽለን በራሳችን ፊደል እንጠቀም የሚለው የአቶ አበበ ረታ ሃሳብ ሳያሸንፍ፣ ታዳሚው የአቶ አበበን ሃሳብ እንቀበለው አንቀበለው እያለ በማመንታት ላይ እንደነበር የሚገልፁት መንግሥቱ ለማ፤ እሳቸው የሚደግፏቸው የነበሩትና ቀደም ሲል በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ በዚሁ ዙሪያ ሲደረግ በነበረው የጦፈ ክርክር፤ የአገራችን ፊደል መነካት የለበትም በማለት ሽንጣቸ...