ልጥፎች

ያዕቆብ ወልደማርያም

ጎምቱ ጋዜጠኛ!__ያዕቆብ ወልደማርያም ************************* ስለ ኢትዮጵያ የጋዜጠኝነት ታሪክ ሲወሳ ስማቸው አብሮ ከሚጠቀሰው ውስጥ ይመደባሉ። የመንግሥታዊው «ዘ ኢትዮጵያን ሄራልድ» ጋዜጣ የመጀመሪያው ኢትዮጽያዊ ዋና አዘጋጅም ሆነው ሰርተዋል - አቶ ያዕቆብ ወልደማርያም። ዛሬም በ86 ዓመታቸው ከሙያው አልራቁም። ያነባሉ፣ ይጽፋሉ፣ በሌላ ሰው የተጻፉትንም ያርማሉ። ይህን ተግባራቸውን የነፍሳቸው ምግብ ያህል የሚቆጥሩት አቶ ያዕቆብ፤ በሚዲያ ራሳቸውን ለማስተዋወቅ ፈቃደኛ አይሆኑም። ስለ ሥራቸውና ማንነታቸውም መናገርን አይሹም። «ታዋቂነትና ዝነኝነት በሥራ እንጂ በቲፎዞ ወይንም በሌሎች ፍላጎትና ግፊት መሆን የለበትም» ብለው ያምናሉ። ይህን እያሰብኩ ከአንድ ወዳጃቸው ስልካቸውን ወስጄ ደወልኩ፤ ስልካቸውን አነሱ። ማንነቴን ገልጬ ለቃለ ምልልስ ቀጠሮ እንዲይዙልኝ ጠየቅሁ። በቀላሉ ፈቃዳቸው ይሆናል ብዬ ባልገምትም በስልክ ንግግራችን ብዙም የማሳመን ጥረቴን ሳልገፋ «የእኔ ታሪክ ለሌሎች የሚጠቅምና የሚያስተምር ከሆነ መልካም፤ ይሁን!» የሚል ምላሻቸውን አገኘሁ። በሦስተኛው ቀን በተቀጣጠርንበት ሰዓት ሽሮ ሜዳ ወደሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ያቀናሁት እኚህን ጎምቱ (በሳልና አንጋፋ) ጋዜጠኛ፣ በአገሪቱ ወሳኝ የታሪክ ምዕራፎች ሁሉ ሃሳባቸውን በብዕራቸው ሲያነጥቡ፤ የሌሎችንም ጽሑፎች ሲያረቱ የነበሩትን አረጋዊ እንዴት ባለ አቅም ቃለ መጠይቅ ማድረግ እንደሚገባ እያሰብኩና እያሰላሰልኩም ነበር። የእርሳቸው አቀራረብ ግን ነገሮችን ሁሉ ቀላል የሚያደርግ ሆነ። ለማንበቢያና ለመጻፊያ ምቹ ሆኖ በተዘጋጀና በመስታወት በተከለለ በረንዳቸው ከሁለት ሰዓት በላይ ባደረግነው ቆይታ የበርካታ ዘመናት ጋዜጠኝነት ሙያዊ አስተዋጿቸውንና የሕይወት ልምዳቸውን እንዲህ አወጉኝ...

አምባሳደር ዘውዴ ረታ ታላቁ የታሪክ ማሕደር ተለየን

ምስል
                                                                 (ከ1927-2008 ዓ.ም) ኢትዮጵያ ሰሞኑን ከባድ ሃዘን መትቷታል። ታላላቅ ሰዎቿን በሞት ተነጥቃለች።  ባለፈው ሳምንት ደግሞ ታላቁን የታሪክ ፀሐፊ ጋዜጠኛ እና ዲኘሎማት አምባሣደር ዘውዴ ረታ አጥታለች።  ዘውዴ ረታ ብሪታኒያ (ለንደን) ውስጥ አረፉ። ከአንድ ወር በፊት ነሀሴ 7 ቀን 2007 ዓም አምባሣደር ዘውዴ ረታ የተወለዱበት የ80 ዓመት የልደት ቀናቸው ነበር። የማስተር ፊልምና ኮሚኒኬሽንስ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ ቢኒያም ከበደ ለኚህ ታላቅ ሰው የሚመጥን ዝግጅት አድርጐ የዘውዴ ረታን የ80 ዓመት የልደት በአላቸውን ጐፋ ገብርኤል በሚገኘው መኖርያ ቤታቸው በደማቅ ሁኔታ አከበረላቸው። እኔም በዚህ የልደት በአላቸው ቀን ተጋብዤ የዘውዴ ረታን የመጨረሻውን የልደት በአል አከበርኩ። ያቺ ቀን ፈጽሞ አትረሣኝም። ምክንያቱም ዘውዴ ረታ ትልቅ ኢትዮጵያዊ የገዘፈ ስብእና ብሎም በሕይወት ያሉ የዘመን ተራኪ ብእረኛ በመሆናቸው ነው። ከእንዲህ አይነት ሰው ጋር ዳቦና ኬክ ቆርሶ መቋደስ፤ የኋላና የፊት የኢትዮጵያን ታሪክ ማውጋት፤ ከቶስ በ...

ባሻ አሸብር በአሜሪካ

ምስል
  ደማሙ ብዕረኛ መንግስቱ ለማ ************************** የዛሬ አስር አመት በታላቅ ሹመት                            አሜሪካ ልኮኝ ነበረ መንግስት ዋሽንግተን ገብቼ ዋልኩ አደርኩኝና ሽር ሽር ስል ሳለ ባንድ አውራ ጎዳና አላፊ አግዳሚውን ጥቁሩን ነጩን ሳለ ስመለከተው በኢትዮጵያዊ አይን የውሀ ጥም ደርሶ ስላረገኝ ቅጥል ከመንገድ ዳር ካለች ካንድ ትንሽ ሆቴል ጎራ አልኩና ገና ከወንበር ላርፍ ስል ተንደርድሮ መጣ የሆቴሉ ጌታ አማረው ቋመጠ ከጀለው ሊማታ አብዷል ሰክሯል እንዴ ምንድን መሆኑ ነው በል ንካኝ በዱላ ግንባርህን ላቡነው ብዬ ስነጋገር ሰምቶ ባማርኛ አሳላፊው ሆነ አስታራቂ ዳኛ ለጥ ብሎ እጅ ነሳና እንደሀገራችን ህግ አክብሮ ጠየቀኝ ምን እንደምፈልግ እኔም ጎራ ያልኩንት የሚጠጣ ነገር ለመሻት መሆኑን ነግሬ ከወንበር ይቅርታዎን ጌታ አዝናለሁ በጣሙ ምናምኒት የለም በከንቱ አይድከሙ አለና እጅ ነሳኝ ሳቁን እየቻለ “ውሀም የለ?” ብለውማ በሳቅ ገነፈለ ቤቱን የሞላው ሰው ሁሉም አጨብጭቦ ብራቮ! ተባለ ብራቮ! ብራቮ!  በጣም ተገርሜ ደንቆኝ አየሁት ከዘራዬን ይዤ ሄድኩኝ ወጣሁት ሃሣብ ገብቶኝ ደጅ ሳሰላስል ቆሜ ያን ቂዛዛ መስኮት ባስተውለው አግድሜ አራዳ ግሪኮች እንደሚሸጡት ያለ በያይነቱ አየሁኝ ብስኩት ትዝ አለኝ “አራዳ አዲስአባ ሆይ ሀገርም እንደሰው ይናፍቃል ወይ?” አስጎመጀኝ በሉ ሳይርበኝ ጠግቤ አስተውለው ጀመረ መስኮቱን ቀርቤ ...

አዛዥ ሐኪም ወርቅነሕ እሸቴ(ዶ/ር ማርቲን)!!

(በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሐኪም) ************************************** በኢትዮጵያና በእንግሊዝ መካከል በኖረው ታሪክ መቸም ቢሆን በማይዘነጋው የመቅደላው ግብግብ በወራሪው ወታደሮች ሳይቀር በሚገባ የተወደሰው የመይሳውን የክብር አሟሟት ባስገኘልን ልዕልና ፋንታ ከዚሕ አስደናቂ ታሪክ ጀርባ በደንብ ያልተነገሩ ብዙ እውነቶች በመኖራቸው አቅም በፈቀደ ታሪካችንን ከያለበት እያሳደድን ማቅረባችንን ስንቀጥል ክብር ይሰማናል….በዚሕ የአጭር አጭር ወግ ሁልጊዜም ቢሆን በቁጭት ከሚያንገበግበን የልዑል ዓለማየሁ ስደትና ሞት ጋር የሚዛመድ የአንድ ታዋቂ ኢትዮጵያዊ ግለ ታሪክ በወፍ በረር ልንቃኝ እድል ቀናን………..በአጼ ቴዎድሮስ የመጨሻዎቹ የሥልጣን ዓመታት በውስጥ ፖለቲካ ምክንያት በመቅደላ አምባ ለእስር የሚጋዙ በርካቶች ነበሩ….ከእነዚሕም መካከል የዛሬው ባለታሪካችን እናትና አባት ነጋድራስ እሸቴና ወ/ሮ ደስታ ወልደማርያም ይገኙበታል…..በ1857 ዓ/ም በጎንደር ከተማ የተወለዱት ወርቅነሕ ገና የሦስት ዓመት ጨቅላ ሳሉ ከወላጆቻቸው ጋር በመቅደላ አምባ ለእስር መደረጋቸው ምን አልባትም የወደፊቱን እጣ ፈንታቸውን ያደላደለ አጋጣሚ መፍጠሩ አልቀረም……በ1860 ዓ/ም የእንግሊዝ ጦር መቅደላን ሲይዝ በተፈጠረው እረብሻ የሞተው ሞቶ የተቀረው እግሬ አውጪኝ ሲል ከተገኙት ሕጻናት መካከል የአጼ ቴዎድሮስ ልጅ ልዑል ዓለማየሁና ሕጻን ወርቅነሕ በእንግሊዝ ወታደሮች ተማርከው ከወራሪው ጦር ጋር ጉዞ ጀመሩ………ከባሕር ወደብ ሲደርሱ ልኡል ዓለማየሁና ሕጻን ወርቅነሕ ሊለያዩ ግድ ሆነ....... ሮበርት ናፔር ልዑል ዓለማየሁን ይዞ ወደ እንግሊዝ ሲያቀና ሕጻን ወርቅነህ ግን ከኮሌኔል ቻርለስ ቻምበርሊን ጋር በመሆን በወቅቱ በእንግሊዝ ቅኝ ግ...

“ኦሮማይ” እና በዓሉ ግርማ

ምስል
ጸሓፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ ******************  ኦሮማይ ከልቡ መጽሐፍ ነው፡፡ በአማርኛ ልብ-ወለድ መጻሕፍት (Novel) ታሪክ በጣም አነጋጋሪውና አከራካሪው መጽሐፍ ነው፡፡ እስከ አሁን ድረስ የህዝብ ፍቅር ካልተነፈጋቸው ጥቂት መጻሕፍት አንዱም ነው፡፡ በህይወቴ ብዙ ጊዜ እየደጋገምኩ ካነበብኳቸው መጻሕፍት መካከልም በመጀመሪያው ረድፍ ይሰለፋል፡፡ ይሁንና ሰዎች ለዚህ መጽሐፍ ያላቸው አድናቆት እንደየ አመለካከታቸው ይለያያል፡፡ መጽሐፉ የብዙዎቹን አትኩሮት የሳበው ታሪኩ እውነት ነው ስለተባለ እና በመጽሐፉ ሳቢያም የደራሲው ህይወት ለአደጋ በመጋለጡ ይመስለኛል፡፡ ከመጽሐፉ ዐቢይ ገጸ-ባህሪያት አንዱ የሆኑት ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ “የደም እምባ” በተሰኘው መጽሐፋቸው ተመሳሳይ እይታ አንጸባርቀዋል፤ እንደ ሻለቃ ዳዊት አባባል ኦሮማይ ባይታገድ ኖሮ ተወዳጅነቱ ይሄን ያህል አይገዝፍ ነበር፡፡ ሆኖም እኔ በዚህ አባባል አልስማማም፡፡ ደራሲው ባይሞት እና ታሪኩ እውነተኛ ባይሆን እንኳ “ኦሮማይ” ተደናቂ የመሆንን እድል አያጣም ነበር ብዬ አምናለሁ፡፡ ለዚህም በርካታ አብነቶችን መጥቀስ ይቻላል፡፡ “ኦሮማይ” በቅድሚያ ቀልብን የሚስበው በአጻጻፍ ብሂሉ ነው፡፡ ደራሲው ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው አጫጭር ዐረፍተ ነገሮችን ይጠቀማል፡፡ ይህም አንባቢው የመጽሐፉን የትረካ ቅደም ተከተል ሳይስት ድርሰቱን ያለድካም እንዲያጣጥም ያግዘዋል፡፡ ደራሲው ጠጣር ሃሳቦችን በቀላሉ ይዘረዝራል፡፡ የዘመኑ መንግሥት አሰራርን ለተደራሲው በሚገባው ቋንቋ ቀለል አድርጎ ያስረዳዋል፡፡ በሌላ በኩል መጽሐፉ ኪናዊ ውበቱን እንዳይስት ደራሲው በእጅጉ ተጠቧል፡፡ ዘይቤአዊ አባባሎችን ከዘመኑ የአነጋገር ፋሽን ጋር እየቀላቀለ አንባቢውን ያዝናናዋል፡፡ በ...

ደራሲ አዳም ረታ

ምስል
  አዳም ረታ በ1950 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ተወለደ። በትምህርት አለም - በጂኦግራፊ የመጀመሪያ ዲግሪውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተቀብሏል። ሁለተኛ (የማስተርስ) ዲግሪውን ደግሞ በውጭ ሀገር አግኝቷል። የሚፅፈው በአብዛኛው አጫጭር ልቦለዶችን ቢሆንም ግጥሞችንም ይፅፋል። በተለያዩ ጊዜያት ግጥሞቹ በተለያዩ መፅሔቶች ላይ ታትመዋል። ያልታተሙ ግጥሞችም አሉት። ከተደራሲው ጋር የተዋወቀበት እና በኢትዮጵያ ስነ ጽሑፍ ተከታታዮችና አንባቢዎች ልብ ውስጥ የመሠረት ድንጋይ ያስቀመጠበት “አባ ደፋር እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች” በኩራዝ አሳታሚ ድርጅት የታተ መው በ1977 ዓ.ም ነው። (በዚህ መድብል ውስጥ አራት ስራዎችን አዋጥቷል፡ “ድብድብ” ፣ “ዕብዱ ሺበሺ”፣ “ሲሮኮ” እና “ሲፊንክስ”) ሜጋ አሳታሚ ድርጅት በ1990 ዓ.ም ባሳተመው “ጭጋግና ጠል” የአጭር ታሪኮች ስብስብ “ዘላን” የተባለው ልቦለዱ ታትሟል። እነዚህ ሁለቱ ከሌሎች ደራሲዎች ስራዎች ጋር የታተሙለት ስለሆነ እንደ ወጥ ሳይቆጠሩ ነው ከላይ የሰፈረው የተባለው። በ1981 ዓ.ም በኩራዝ አሳታሚ የታተመው “ማህሌት” የደራሲው የመጀመሪያ ወጥ የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ መፅሀፍ ነው። በሻማ ቡክስ በ1997 ዓ.ም የታተመው “ግራጫ ቃጭሎች” እንደ ብሉይ (classic) ሥራ ሊታይ የሚችልና የደራሲው ልዩ ብቃት የታየበት ወጥ ረጅም ልብወለድ ነው። በ2001 ዓ.ም ሁለት ልዩ ስራዎች ይዞ የቀረበው አዳም፡ የአጫጭር ልብወለዶች ስብስብ የሆነው “አለንጋና ምስር” እና እርስ በርሳቸው በቀጭን የታሪክ ክር የሚገናኙ ልብወለዶች (ኖቬላዎች) ያካተተው “እቴሜቴ የሎሚ ሽታ” ለአንባቢያን አበርክቷል። በቀጠሉት ሦስት ዓመታት በየዓመቱ አንዳንድ መፅሐፍ ለአንባቢያ ያደረሰ ሲሆን በ2...

ያወጣሁ ያወረድኩት ሀሳብ

ምስል
Chasing Beautiful Questions  እንዲህ አሰብኩ ። ሜኒያፖሊስ አየር መንገድ የአይሮፕላኑ መንደርደሪያ መስክ ላይ እኔን እና ብዙ ፈረንጆችን የተሳፈርንበት የብረት አሞራ ወደ ሰማይ ለመምጠቅ ሲንደረደር አንድ ሀሳብ ወደ አእምሮዮ መጣ።እሳቤውን የጫረልኝ አንድ እግሩን በቀን ጎዶሎ ያጣ ፈረንጅ ነው። ገና የ 21 ዓመት ጐረምሳ ሳለ በበጋው ወራት አሪዞና ውቅያኖስ ዳርቻ ፈረንጆቹ ዋተር እስኪንግ የሚሉትን በእኛ አገር እይታ ቅብጠት በእነሱ ደግም እስፓርት ጨዋታ ላይ እንዳለ ያልታሰበ የሞተር ጀልባ ገጭቶት እራሱን ይስታል ። እራሱን ያወቀው እሆስፒታል ውስጥ ነበረ ። መመልከት አልፈልግም ግን ልመልከተው አለ ግራ እግሩ ተቆርጧል እጂግ ልብን የሚሰብር ሀዘን ነበር። የሆስፒታሉ ፕሮስቴቲክ ወይም የሰው ሰራሽ እግር ሞያተኞች በአሉሚኒየም የተሠራ እግር አመጡለት እናም ከብዙ ማስጠንቀቂታያ ጋር ከሆስፒታል ወጣ። ለመጀመርያ ጊዜ በአዲሱ ሰው ሠራሽ እግር ለመራመድ ሲውተረተር እንደ ጐማ ተጠቅልሎ ነበር የወደቀው ።ከዚያች ሰከንድ በኋላ ዳግመኛ እንዲህ አይነት ቅብጠት እንደማያዋጣ ገባው ።ዶክተሮቹ በቀን ሁለት ጊዜ ያውም ብዙ ነገር እየተደገፈ እዲሞክር ቢያዙትም እርሱ አሻፈረኝ ብሎ ከደንቡ ውጪ ልራመድ ሲል ነው ዋጋውን ያገኘው። ፊሊፕ የተባለው ይህ ጀብደኛ ጕረምሳ ጭራሹኑ የእግሩን መቆረጥ አላምንም ማለቱ ነበር በጊዜው ብዙውችን ግራ ያጋባው ።የእጮኛው አባት አይዞህ ፊሊፕዬ እስክትለምደው ድረስ ነው ከትንሽ ጊዜ በኋላ ትቀበለዋለህ አለው።እርሱ ግን የእግሩን አለመኖር ማመን አልቻለም ።ከንፈሬን በንዴት ነከስኩት ይላል ፊሊፕ ።እውነቱን ነው ማንም ሰው በሚረዳበት አረዳድ ከወሰድነው እግሬ ተቆርጧል ብዬ ከማመን ውጪ አማራጭ የለኝም ግን...